Shalom Medical Consultancy

Shalom Medical Consultancy This page is created to promote helath realted issues and provide medical consultation for pateints

08/07/2022

"የተሰራልኝ ኦፕሬሽን ምን እንደነበር እና ለምን እንደ ተሰራልኝ አላውቀውም!"

ከተለመዱት የአዳር የስራ ፕሮግራሜ በአንዱ ነው... አንድ በ40 ዎቹ እድሜ ክልል ውስጥ ያለ ጎልማሳ በጠና ታሞ ወደ ቀዶ ህክምና ድንገተኛ ህክምና ክፍል መምጣቱ ተነግሮን እሱን ለማየት ሄድን።
ገና ሲታይ በጽኑ ህመም መታመሙ ያስታውቃል። ያቃስታል...ሆዱ በጣም ከመቆዘሩ የተነሳ የደረሰች ነፍሰ ጡር አስመስሎታል። ቀርበን ካየነው በኋላ መደ መመርመርያ ክፍል አስገብተን ጫጫታ በሌለበት ሁኔታ ስለ ህመሙ ሁኔታ መጠየቅ ጀመርን። ህመሙ ሦሥት ቀን እንደሆነው ...በእነዚህ ቀናትም... እያደር የሆዱ መቆዘር እና ቁርጠት እየጨመረ መምጣቱን በተያያዘም እንደሚያስመልሰው እና ሰገራም ሆነ ፈስ እንዳልወጣው ነገረን። ሌሎች አስፈላጊ ምልክቶች እንዳሉት እና እንደሌሉት ከጠየቅን በኋላ.... ሰውነቱን ለመመርመር ልብሱን እንዲገልጥ ጠይቀን ምርመራው ተጀመረ። ሆዱ ላይ ቁልቁል በእንብርቱ የሚያልፍ የቆየ የኦፕሬሽን የሚመስል ጠባሳ አለ። የበፊቱ ኦፕሬሽን በሌላ ሀስፒታል የተሰራ በመሆኑ አሁን ስለያዘው በሽታ ምንነት ለማወቅ ፍንጭ ስለሚሰጠን እንደገና መጠየቅ ጀመርን።
"ይሄ መቼ የተሰራ ኦፕሬሽን ነው?"
" የዛሬ አምስት ዓመት አካባቢ ነው" አለ እያቃሰተ።
" በምን ምክንያት ነበር የተሠራው ኦፕሬሽኑ?" ቀጣዩ እና አስፈላጊው ጥያቄ ተጠየቀ።
"እሱን አላውቀውም.... ብቻ ያኔም እንዳሁኑ ሆዴን በጣም ታምሜ ነው በድንገተኛ የተሰራልኝ" አለ የምርመራ አልጋው ላይ እየተገላበጠ።
" ስለ ህመሙ ምንነት ተነግሮህ ነበር?....ከኦፕሬሽኑ በኋላስ ለምርመራ የተላከ ናሙና ነበር? ...... የዛን ጊዜም ካሁኑ ህመምህ ጋር ተመሳሳይ ምልክቶች ናቸው የነበሩት?...ወዘተ "
ስለ በፊቱ ኦፕሬሽን ብዙ ጥያቄዎችን አከታትለን ብንጠይቅም...ከታማሚውም ሆነ ከአስታማሚዎቹ በቂ መረጃ ማግኘት አልቻልንም ነበር። አሁን ስላለው ህመሙ ለማወቅ ትልቁን እና ዋናውን መረጃ ማግኘት ሳንችል ቀረን። የአካል ምርመራውን ከጨረስን በኋላ አስፈላጊ የራጅ እና የላብራቶሪ ምርመራዎችን ልከን ኦፕሬሽን የሚያስፈልገው ህመም ነበር እና በዚህም ከተስማማን በኋላ ይዘነው ወደ ኦፕሬሽን ገባን።

ለመሆኑ ....
1. አንድ ታካሚ ኦፕሬሽን ሊሰራለት ሲወሰን ስለ በሽታው ምንነት የመጠየቅ መብት አለው?
2. ኦፕሬሽን ለምን እነደሚሰራለት እንዲሁም ኦፕሬሽን ባይሰራ ሌላ የህክምና አማራጭ እንዳለው የመጠየቅስ መብት አለው?
3. ኦፕሬሽኑን ተከትሎ ሊመጡ ስለሚችሉ ተያያዥ ችግሮችስ ማብራርያ ሊደረግ ይገባል?
4. ኦፕሬሽኑን የሚሰራው ባለሞያስ ስለ በሽታው እና ስላሉት የህክምና አማራጮች እንዲሁም ተያይዘው ስለሚመጡ ችግሮች ለታካሚው እና ቤተሰቡ ማብራርያ የመሰጠት ግዴታ አለበት?

እነዚህን ከላይ የተዘረዘሩትን ጥያቄዎች የሚመልስልን ማንኛውም ኦፕሬሽን (መለስተኛም ሆነ ከባድ) ከመሰራቱ በፊት በኦፕሬሽን ባለሞያው እና በታካሚው( ቤተሰቡ) መኃል የሚደረገው የስምምነት ቅጽ(Consent form) ነው።
ይህ የስምምነት ቅጽ በተለያዩ ሆስፒታሎች መጠነኛ የይዘት ልዩነት ቢኖረውም ከሞላ ጎደል ወሳኝ በሆኑ ነጥቦች ላይ ሁሉም ተመሳሳይ ይዘት አላቸው።
የቅድመ ኦፕሬሽን የስምምነት ቅጽ ታካሚው እና ቤተሰቡ በቅጹ ላይ ከመፈረማቸው በፊት መሞላት ያለበቸውን አስፈላጊ ጥያቄዎችን ይይዛል። ከእነዚህም መኃል የሚከተሉት ይገኙበታል።
፨ ኦፕሬሽኑ የሚሰራለት ታካሚ ስም....
፨ ኦፕሬሽኑን የሚሰራው ባለሞያ/ዎች ስም....
፨ ታካሚው(ቤተሠቡ) ስለ በሽታው ምንነት ያውቃሉ ወይስ አያውቁም ......
፨ በሽታው ምንድን ነው....
፨ ኦፕሬሽኑ የሚሰራው በምን ምክንያት ነው? .....
፨ በኦፕሬሽኑ ምክንያት ሊከሰቱ የሚችሉ ችግሮች ምንድን ናቸው?...
፨ ከኦፕሬሽን ውጪ ሌላ የህክምና አማራጭ አለው ወይ? ....
፨ ኦፕሬሽን ባይሰራ ሊመጡ የሚችሉ ችግሮች ምን ምን ናቸው?....
፨ በኦፕሬሽኑ ሰዓት ታካሚው ደም ቢያስፈልገው ለመውሰድ ፈቃደኛ ነው ወይ?...... እና ወዘተ

ማንኛውም ታካሚ ድንገተኛም ሆነ ድንገተኛ ላልሆነ ህመም፤ መለስተኛም ሆነ ከባድ ኦፕሬሽን ከማሰራቱ በፊት ከላይ የተዘረዘሩትን ነገሮች ኦፕሬሽኑን ከሚሰራው ባለሞያ ጠይቆ የመረዳት መብት አለው። ባለሞያውም ስምምነቱን ከማስፈረሙ አሥቀድሞ እነዚህን እና ሌሎች ጠቃሚ መረጃዎችን ለታካሚው እና ቤተሰቡ የማስረዳት ግዴታ አለበት። ይህን ማድረጉ አሁን አሁን እየታየ ያለውን በታካሚ እና በባለሞያው መኃል ያለ አለመተማመን.... እና አስፈላጊም ሆነ አላስፈላጊ መወነጃጀል ሊቀንስ ይችላል። በተለምዶም ከህክምናው በኋላ የሚከሰቱ ችግሮችን ታካሚው እና ቤተሰቡ... እንዲሁም ዩቲዩበሮች... "የህክምና ስህተት ነው" እያሉ ጣታቸውን ወደ ባለሞያው እንዳይቀስሩ የራሱ ትልቅ ሚና ይኖረዋል። በማንኛውም መለስተኛም ሆነ ከባድ ኦፕሬሽን ወቅት የታካሚውን እና ቤተሰቡን መልካም ፈቃድ ያማከለ ኦፕሬሽን መሰራት እንዳለበትም ግንዛቤን ይፈጥራል።

የማንኮራፋት ችግር | Snoring disorder     "የማንኮራፋት ችግር ማህበራዊ ጫና ከመፍጠሩ ባሻገር ጤና ላይ የሚያመጣዉ መዘዝ የጎላ ነው።የማንኮራፋት ችግር የሚከሠተዉ አየር ከሳንባ ...
12/05/2022

የማንኮራፋት ችግር | Snoring disorder

"የማንኮራፋት ችግር ማህበራዊ ጫና ከመፍጠሩ ባሻገር ጤና ላይ የሚያመጣዉ መዘዝ የጎላ ነው።

የማንኮራፋት ችግር የሚከሠተዉ አየር ከሳንባ ወይም ወደ ሳንባ በሚወጣበት እና በሚገባበት ጊዜ በሚያልፍባቸው የአየር ቱቦ በቂ የሆነ ክፍተት ካላገኘ ወይም የሚያልፍበትን የተመቻቸ መስመር የሚያስቀይር ችግር ካጋጠመው የሚፈጥረው የተዛባ ድምጽ (turbulent air flow) ነው።

ይህን የማንኮራፋት ችግር የሚያስከትሉ ምክነያቶች በህጻናት እና አዋቂዎች ላይ የተለያዩ ቢሆንም የሚከሠቱበትን ቦታ በ 4 ከፍሎ ማየት ይቻላል።

1. ከአፍንጫ እስከ ላንቃ ያለው የአየር መተላለፊያ ሲሆን ህጻናት ላይ በአብዛኛው አዴኖይድ የምንለው የቶንሲል ክፍል መጠን መጨመርና በአፍንጫ የሚያልፈውን አየር ሲዘጋ የሚከሠት ነው። አዋቂወች ላይ ከዚህ ቦታ በሚነሳ ችግር ማንኮራፋት ከተከሠተ ካንሠርን ጨምሮ ሌሎች እብጠቶችን ማሠብ እና ምርመራ ማድረግ ግድ ይላል።

2. ከምላስ የኋለኛው ክፍል እና በጎኑ ከሚገኙ ቶንሲሎች (posterior tounge and palataine tonsilar hypertrophy) ጋር ተያይዞ የሚከሠት ማንኮራፍት ነው። የዚህ ከምላስ ጎን የሚገኘው ቶንሲል የማንኮራፍት ችግር ከመፍጠሩ በላይ በ ተደጋጋሚ የቫይረስ እና የባክቴሪያ ኢንፌክሽን በመፍጠር ተጨማር የጤና እክል ያስከትላል።

3. በአፍና መንገጭላ አካባቢ የሚከሠቱ የአፈጣጠር ችግሮች እንዲሁም ከነዚህ ቦታወች ተነስተው የኅለኛውን የአየር መተላላፊያ ሊዘጉ የሚችሉ እብጠቶች እንደ ምከንያት ይጠቀሳሉ።

4. የኋለኛው የአየርና የምግብ የጋራ መተላለፊያ ግድግዳን የሚሠሩ ጡንቻወች መዛል ፣ በስብ መሞላት ፣ በእብጠት መጠቃት ወይም መግል መቋጠር ከተፈጠረ የሚከሠት ይሆናል።

ማንኮራፍት የሚከሠትባቸውን ምክነያቶች በወፍ ዘረር ካየን የዚህ ችግር መጠን ከሠው ሠው እንደተፈጠረው የአየር መተላለፊያ መስመር መጥበብ መጠን ይለያያል። ይሔም ከልማዳዊ ማንኮራፍት (habitual snorer) እስከ ሳንባ ከረጢቶች መጠን መቀነስ (pulmonary alveolar hypoplasia) ብሎም የሳንባ ደም ስሮች ግፊት እና የልብ ችግር ሊፈጥር ይችላል።

በተጨማሪም አካላዊና አእምሯዊ የእድገት ችግር ፣ የጸባይ ችግር (በተለይም ህጻናት ላይ) ፣ ቀን አብዝቶ የመተኛት ችግር ፣ በስራ የመዛልና ውጤታማ ያለመሆን እና የመሳሠሉ ተጽኖወችን ይፈጥራል።

በትዳር አጋር ላይ የሚፈጥረው ጫና እና ማህበራዊ ቀውሡም ሌላው ጉዳቱ ነው። ማንኮራፍት የፈጠረውን የጤና ችግር ደረጃ ለማወቅ አይነተኛ የሚባለው መሣሪያ (polysomnography ) ሲሆን በሀገራችን የለም ማለት ይቀላል። ነገር ግን ይሔንን ለመተካት የሚፈጠሩ ስሜቶችን እና ምልክቶችን በማየት እና የልብ ፣ የአተነፋፈስ ምርመራወችን በማድረግ ደረጃውን ማወቅ ይቻላል። የዚህን ጀረጃ ማወቁ ጥቅሙ ለእያንዳንዱ ደረጃ የሚሠጠው ህክምና የተለያየ መሆኑ ነዉ።

ወደ መፍትሔው ስንመጣ ፤ መፍትሔው የሚወሠነው ማንኮራፍቱን በፈጠረው ችግር እና የችግሩ መጠን ሲሆን

1. በአብዛኞች ህጻናት ላይ ከአፍንጫ ጀርባ እና ከምላስ ጎን ያለውን ቶንሲል በሠርጀሪ በማስወገድ የሚስተካከል ይሆናል።

2. በአዋቂወች ደግሞ እባጮች (እጢወች) እንደሌሉ ከተረጋገጠ በኋላ ክብደት መቀነስ ፣ የኦክስጅን ህክምና (CPAP) ብሎም የአየር መተላለፊያን ቱቦ ለማሥፍት የ ሚደረጉ ሠርጀሪወች (uvuloplalatopharyngoplasty
,uppp እና ሌሎች ዘርፈ ብዙ ሠርጀሪወች) የህክምና አማራጮች ናቸው።

ስለዚህ፦ ማንኮራፋትን እንደ ቀላል ችግር በማየት አንዘናጋ፤ቢያንስ ያለንበት የማንኮራፍት ጀረጃ በምን መሥተካከል እንደሚችል ሀኪሞችን እናማክር።"

ዶ/ር አለማየሁ እሸት (ከአንገት በላይ ስፔሻሊስት ፣ መምህር እና ረዳት ኘሮፌሰር )
Via

"ህፃናት መች ነው ጥርስ ማብቀል ያለባቸው?" "ህፃናት እስከ መች መብቀል አለበት? ካልበቀለ መች ወደ ባለሙያ መመሄድ አለባቸው? የጥርስ መብቀል ከተቅማጥ በሽታ ጋር ይገናኝ ይሆን? ስለ ህፃ...
11/05/2022

"ህፃናት መች ነው ጥርስ ማብቀል ያለባቸው?"

"ህፃናት እስከ መች መብቀል አለበት? ካልበቀለ መች ወደ ባለሙያ መመሄድ አለባቸው? የጥርስ መብቀል ከተቅማጥ በሽታ ጋር ይገናኝ ይሆን? ስለ ህፃናት የጥርስ እድገት ትንሽ ጀባ ልበላችሁ

ብዙ እናቶች ልጆቻቸው ጥርስ መች ማብቀል እንደሚጀምሩ በግልፅ ስለማያውቁ ልጄ እስካሁን ጥርስ አላበቀለም/ አላበቀለችም ብለው ጤና ተቋም ሲመጡ ማየት የተለመደ ነገር ነው። አንዳንድ እናቶች ደግሞ እስከመች ድረስ ሊያድግ እንደሚችል አያውቁም በዚህ የተነሳ እራሳቸውን ሲያጨናንቁ እናያለን ይህን ጭንቀታቸውን ለመቅረፍ እኔም ካነበብኩት ትንሽ ጀባ አልኳችሁ።

የህፃናት የጥርስ እድገት በጨቅላዎች እና በልጆችዎ ድድ ውስጥ የጥርስ መብቀልን ያመለክታል ይህ የሚጀምረው ብዙውን ጊዜ ልጅዎ ከ6 እስከ 8 ወር ዕድሜ ሲኖረው ሲሆን፡፡ ልጅዎ የ30 ወራት ዕድሜ ላይ ሲደርስ ሁሉም 20 የህጻናት ጥርሶች ቦታቸውን ይይዛሉ ፡፡

አንዳንድ ልጆች ግን ከ8 ወር ዕድሜያቸው በሗላም ቢሆንም ምንም አይነት ጥርስ ላያሳዩ ይችላሉ ፣ ይህ ግን ብዙውን ጊዜ የተለመደ ቢሆንም ምንም ጥርስ አስከ 13 ወር ካልበቀለ ለባለሙያ ማሳየት ይገባል፡፡

ብዙውን ጊዜ ሁለቱ የታችኛው የፊት ጥርሶች (የታችኛው ኢንሲዘሮች) ቀድመው ይበቅላሉ፡፡ ቀጥለው ሁለቱ የላይኛው የፊት ጥርሶች (የላይኛው ኢንሲዘሮች) ያድጋሉ፡፡

ከዚያም ሌሎች ወተት ጥርሶች (ኢንሲዘሮች) ፣ የላይኛውና የታችኛው መንጋጋዎች ፣ የውሻ ክራንቻዎች፣ በመጨረሻም የላይኛውና የታችኛው በጥልቀት የሚገኙት መንጋጋዎች ይበቅላሉ፡፡

ልከጆች ጥርስ ማብቀል ሲጀምሩ ምን አይነት ምልክቶች ያሳያሉ ??

- መነጫነጭ ወይም ብስጩነት ማሳየት
- ጠንካራ ነገሮችን መንከስ ወይም ማኘክ
- ልጋግ ማዝረብረብ ብዙውን ጊዜ ጥርስ ማደግ ከመጀመሩ በፊት የሚከሰት ነው
- የድድ ማበጥና መጠንከር
- ምግብ እምቢ ማለት
- የእንቅልፍ ለመተኛት መቸገር

መፍትሄውስ ምን ይሆን?

በዚህ ጊዜ ማድረግ ያለብን ልጅዎ የማያኝካቸው ቀዝቃዛ ነገሮች መስጠት። ለልጅዎ ለስለስ ያሉ ምግብ ይስጦቸው ፤ በቀስታ ጥርስ የሚበቅልበት ቦታ በእጅ መንካት። በዚህ መንገድ የልጅዎን የጥርስ እድገት አብረው በመሆን የተሳካ ያድርጉላቸው።"

"መልካሙን ሁሉ ተመኘው"
ዶ/ር መሐመድ በሽር (የህፃናት ሐኪም)
Via Hakim

ቀኟን የተቀማችው ተዳጊ!እድሜዋ 8 ዓመት ነው። አንድ ቀን ከቤተሠቧ ገር በባጃጅ ተሳፍራ ስትጓዝ ባጃጇ ተገልብጣ በደረሰባት ጉዳት የቀኝ እጇ አጥንት በትከሸዋ እና በክርኗ መሀል ይሰበራል። ከ...
08/02/2021

ቀኟን የተቀማችው ተዳጊ!
እድሜዋ 8 ዓመት ነው። አንድ ቀን ከቤተሠቧ ገር በባጃጅ ተሳፍራ ስትጓዝ ባጃጇ ተገልብጣ በደረሰባት ጉዳት የቀኝ እጇ አጥንት በትከሸዋ እና በክርኗ መሀል ይሰበራል። ከአደጋው በኋላ ግን ወላጆቿ ይህችን ህጻን ወደ ጤና ተቋም በመውሰድ ተገቢውን ህክምና እንድታገኝ ከማረግ ይልቅ ወደ መንደር ወጌሻ ይወስዷትና ያሻውን እንዲያደርግ ይፈቅዱለታል። ያ ወጌሻም የሚያደርገውን አድርጎ ሲጨርስ... ሰባራውን እጇን ጥፍንግ አድርጎ ያስረውና ያሰናብታቸዋል። ከቀናት በኋላም የቀኝ እጇ ማበጥ እና ጣቶቿም መጥቆር ጀመሩ። ይህም ወደ ላይ እየሰፋ ሄዶ መጥቆሩ ክርኗን ማለፍ ሲጀምር ወደ ጤና ተቋም ይዘዋት ይመጣሉ። የዚህች ታዳጊ መጨረሻም እሷን ለማትረፍ ጋንግሪን የሰራውን (የጠቆረውን) እጇን መቁረጥ ይሆንና የቀኝ እጇን አጣች። በወላጆቿ ቸልተኝነት፣ በመንደር ወጌሻዎች ከልካይ ማጣት እና አላዋቂነት የዚህች ህጻን እጣ ፈንታ አካል ጉዳተኝነት ሆነ። በቀላል ህክምና በተገቢው የጤና ባለሞያ ታይቶ ሊዲን የሚችል ስብራት እድሜ ልኳን አብሯት የሚኖር ጠባሳ እንዲተውላት ተደረገ።
በተለይ በገጠር አካባቢ ያሉ የጤና ባለሞያዎች.... እና መገናኛ ብዙሃን ህብረተሰቡን በዚህና መሰል ጉዳዮች መረጃ በመስጠት ማስተማር እና ግንዘቤ መፍጠር ያስፈልጋል።

Daai'ma mirga ishee dhabde!

Umuriin ishee saddeeti.Guyyaa tokko maatii ishee waliin Baajaajii dhaan osoo deemaa jirtuu baajaajin garagaluu ishiitin harka mirga ishee irraa lafeen jalaa caba.Maatin ishees yeroo sana gara dhaabbata fayyaa geessuu dhiisanii gara wageeshaa ollaa isaanii geessun namtichi harka ishee akka fedhe akka inni godhu hayyama kennaniif. Innis hojii isaa hojjatee harka ishee jabeessee hidhuun gaggeesse. Guyyoota muraasa booda harki mirga ishee dhiitahuu fi quboonni ishees gurraacha'uu eegalan. Gurraachinni harka ishee kunis gara olii bal'achuun yommuu ciqilee isheerra darbu gara dhaabbata fayyaa fidanii dhufan. Lubbuu ishee baraaruf furmaanni jiru harka ishee gurraacha'ee du'e san ciqilee olitti muruu ta'e. Wallaalummaa maatii isheefii itti gaafatamuu dhabuu wageeshaa sanaatin daa'imti tun harka ishee akka dhabdu taate. Waldhaansa ogeessa fayyaatin salphaati cabni fayyuu danda'u harki ishee akka muramu taasise.
Ogeeyyin fayyaa baadiyyaa keessa hojjatan akkasumas midiyaaleen garaagaraa waa'ee dhimma akkanaarrati uummataaf barumsa dabarsuufii hubannoo laachun barbaachisaa dha.

Pictures taken with consent.

05/04/2020

ሁለት ሰዎችን በኮሮና በሽታ አጥተናል። ይህም የባለሞያ ምክርን ቸል በማለት ለተዘናጋን ሰዎች የማንቅያ ደወል መሆን አለበት። አስፈላጊውን ጥንቃቄ በማድረግ መከላከል በምንችለው በሽታ መሞት አይገባም!

Namoota lama dhukkuba Koronaatiin dhabneera. Kunis warra gorsa ogeessaa dhagahuu didnee of eeguu irraanfanneef dhaamsa guddaa dha. Himan didduun du'a hin diddu akka jedhame akkan hin taane of eeguu hin dagatinaa.

Dhaabbanni Fayyaa Addunyaa  waa'ee itti fayyadamina Maaskii fuulaa ilaalchisee qajeelchi baase kanneen armaan gadiiti.Ma...
01/04/2020

Dhaabbanni Fayyaa Addunyaa waa'ee itti fayyadamina Maaskii fuulaa ilaalchisee qajeelchi baase kanneen armaan gadiiti.

Maaskii fuulaa yoom fayyadamuu qabna?
1. Nama fayyaa yoo taatan Maaskii fuulaa kana kan fayyadamuu qabdan nama dhukkubichaan qabame bira yoo jiraattani dha.
2. Kan isin qufaasisuufi kan isin haxxinfachiisu yoo ta'e maaskii fayyadamuu qabdu.
3. Maaskii fayyadamuun bu'aa guddaa kan qabaatu yoo harka keenyas bishaanii fi saamunaan ykn keemikaala alkoolii qabuun harka keenya dafnee dafnee yoo qulqulleesine qofa.

Maaskii akkamitti ofitti haa keenyu?
1. Maaskii osoo hin kaawwatin dura harka keenya akka armaan olitti ibsametti sirriitti qulqulleessuu qabna.
2. Afaanii fi funyaan keenya sirriitti haguuguu fi fuula keenyaa fi maaskii gidduu fageenyi akka hin jirre mirkaneessuu.
3. Maaskii erga kaawwannee booda harka keenyaan tuttuquum nurra hin jiru. Yommui maaskichi jiidhes ofirraa baasnee bakka isaaf qophaa'etti gatuu qabna.Irra deebinee fayyadamuu hin qabnu.
4. Maaskicha yoo ofirraa baafnu dura gurra keenya irraa baasnee gatuun dafnee harka keenya bishaanii fi saamunaan dhiqachuun nurra jiraata.

01/04/2020

የዓለም ጤና ድርጅት በፊት ማስክ አጠቃቀም ዙርያ ያወጣቸው መመርያዎች የሚከተሉት ናቸው።

?

1. ጤነኛ ከሆኑ ማስክ መጠቀም ያለቦት በበሽታው የተጠቁ ሰዎችን የሚንከባከቡ ከሆነ ወይም አጠገቦ ታማሚ ካለ ነው።
2. የሚያስሎት ወይም የሚያስነጥሶት ከሆነ ማስክ መጠቀም አለብዎት።
3. ማስክ መጠቀም ውጤታማ የሚሆነው የእጃችንን ንጽህና በተደጋጋሚ በውሃ እና በሳሙና ወይም አልኮል ባለው የእጅ ንጽህና መጠበቂያ ውህድ በአግባቡ እጃችንን በማሸት ከተጠቀምን ነው።

?

1. ማስክ ከማጥለቃችን በፊት እጆቻችንን በውሃ እና በሳሙና ወይም አልኮል ባለው የእጅ ማጽጃ ውህድ ማጽዳት አለብን።
2. አፍ እና አፍንጫችንን በአግባቡ መሸፈን እና በማስኩ እና በፊታችን መሃል ክፍተት አለመኖሩን ማረጋገጥ።
3. ማስኩን ካጠለቅን በኋላ በእጃችን መንካት የለብንም እንዲሁም ማስኩ እርጥበት ከያዘ አውልቀን በተገቢው ቦታ መጣል አለብን። መልሶ መጠቀም አይመከርም።
4. ማስኩን ስናወልቅ መጀመርያ ከአንዱ ጆሯችን በማላቀቅ አውልቀን መጣል እና እጃችንን ወድያው መታጠብ አለብን።

30/03/2020

በሀገራችን እስካሁን ድረስ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 23 ደርሷል። ከእነዙህ ሁለቱ ከበሽታው ሙሉ በሙሉ ማገገም የቻሉ ሲሆን ቀሪዎች የህክምና ክትትል እየተደረገላቸው ይገኛሉ።

ነገር ግን ከጤና ሚኒስቴር እና ከባለሞያዎች የሚነገሩንን የበሽታው መከላከያ ዘዴዎች በአግባቡ በመተግበር እራሳችንን እና ሌሎች ወገኖቸችንን ልንጠብቅ ይገባል።

Hanga ammaatti biyya keenya keessatti namoonni dhukkubni qabaman lakkoofsan 23 gahanii jiru. Isaan keessaa namoonni lama guutumaan guututti kan itti wayyaa'e yoo ta'u kanneen hafan immoo gargaarsa ogeessaa argachaa jiiru.

Haa ta'u malee maloota mijisteerri fayyaa fo ogeessoni fayyaa nutti himan kan dhukkubicha ofirraa ittisuuf nu gargaaran sirnaan itti fayyadamuun ofii keenya fi lammiillee keenya dhukkuba kanarraa eegun nurraa eegama.



Send a message to learn more

ከሀገራችን ነባራዊ ሁኔታ አንጻር   በሽታ ስርጭትን ለመከላከል የሚረዱን ዘዴዎች በፎቶዎቹ ለይ የተዘረዘሩት ሆነው በተጨማሪም 1. ሰዎች ከሚበዙባቸው ስፍራዎች ( የእምነት ቦታ፣ ገበያ፣ ወዘተ...
13/03/2020

ከሀገራችን ነባራዊ ሁኔታ አንጻር በሽታ ስርጭትን ለመከላከል የሚረዱን ዘዴዎች በፎቶዎቹ ለይ የተዘረዘሩት ሆነው በተጨማሪም
1. ሰዎች ከሚበዙባቸው ስፍራዎች ( የእምነት ቦታ፣ ገበያ፣ ወዘተ) በተቻለ መጠን መራቅ እና በግል ስፍራ ማካሄድ

2. የህዝብ ትራንስፖርት በተቻለ መጠን አለመጠቀም የግድ ከሆነም እንደተለመደው ከመጠን በላይ እንዳይጭን ጫና ማሳደር። የሰው እጅ በብዛት የሚነካቸውን መደገፍያዎች አለመንካት እናም ከተቻለ አጭር መንገድን በእግር መጓዝ ማዘውተር

3. ምልክቶቹ ሲታዩብን ያለ ምንም ፍርሃት ለሚመለከተው አካል በመደወል ማሳወቅ እና ተገቢውን እርዳታ ማግኘት

4. ፈጣሪ ይጠብቀኛል ብሎ ሁሉን በእርሱ ላይ ጥሎ ከመዘናጋት ይልቅ እኛም ቸልተኛ ሳንሆን አስፈላጊውን እና ቀላል የሆኑትን ጥንቃቄዎች ማድረግ ተገቢ ነው!

Haala yeroo biyyi teenya keessa jirturraa kaanee daandiiwwan dhukkubni vaayirasii kun ittiin daddarbu kanaa gaditti suuraadhan kan ibsaman akkuma jiranitti ta'ee dabalataanis
1. Bakkeewwan namoonni itti baay'atan( manneen amantaa , Gabaa,kkf) irraa of fageessuu

2. Tiraanispoortii uummataa hanga danda'ameen fayyadamuu dhiisuu, yoo dirqama ta'es akkuma baranitti humnaa ol nama baay'ee akka hin feene dhiibbaa irratti uumuu. Hirkoowwan konkolaataa keessaa kan namni baay'en harkaan tuqu irraa of fageessuu akkasumas daandii gabaabaa tahe lafoo deemuu

3. Yoo mallaattoowwan dhukkubichaa ofirratti arginu sodaa tokko malee qaama dhimmi ilaaluf beeksisuun gargaarsa barbaachisaa tahe argachuu

4. Waaqayyo na eega jennee hunda isarratti dhiisnee of dagachuurra nutis of eeggannoo sasalphaa ofiif godhachuu qabnu goone dhibee kanaraa of eegun barbaachisaa dha.

10/02/2020

Address

Swazeeland Street
Addis Ababa
1271

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Shalom Medical Consultancy posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Shalom Medical Consultancy:

Share