13/04/2026
የዘንድሮን የጌታችን የመድኃኒታችንን የኢየሱስ ክርስቶስ የትንሳኤ በአልን ከትብብር ለኢትዮጰያ አንድነት የበላይ አመራሮች ጋር አንድ ላይ በመሆን በቂሊንጦ እስር ቤት ውስጥ ከሚገኙት የህሌና ና የግፍ እስረኞች ከሆኑት ከአማራ ሙህራን እና ጋዜጠኞች እንዲሁም የሰባዊ መብት ተማጋቾች ጋር በማሳለፊ እጅግ ትልቅ ኩራት ይሰማኛል:: ካሳለፍኃቸው ብዙ የፋሲካ በአላትም በአይነቱ ወርቃማ ና የተለየ ያደርገዋል!
በሂደቱም ካስተዋልኳቸው ሁነቶች ውስጥ ከእያንዳንዳቸው ወንድሞች በግልፅ የሚነበብ የስነ ልቦና ጥንካሬ ና ያይበገሬነት የመንፈስ ዕናት እንዲሁም የሚንቦገቦግ የወንድም ና የሀገር ፍቅርን ማየት ችያለሁ!
በዚህ ሂደት ውስጥ እድሉን አግገኝቼ ከአወጋኃቸው ወንድሞቼ መካከል የሚከተሉት ይገኙበታል
1. የተከበሩ ክርስቲያን ታደለ
2. የተከበሩ ዮሐንስ ቡያለው
3. የተከበሩ ዶ/ር ካሳ ተሻገር
4. ዶ/ር ቴዎድረስ ኃ/ማሪያም
5. ዶ/ር ሲሳይ አውግቼው
6. ረዳት ፕ/ሮ ማረጉ ብያብን
7. ዶ/ር ጫኔ ከበደ
8. ጋዜጠኛ ጎበዜ ሲሳይ
9. ጋዜጠኛ ዳዊት በጋሻው…ና የመሳሰሉት የሀገር የቁርጥ ቀን ልጆች ይገኙበታል!
በመጨረሻም ለሀገራችን ሹማምንቶች ማሳሰብ የምፈልገው ሩቅ እንዳታስቡ ወይም እንዳታዩ አይናቸውን የጋረደውን ጉም እግዚአብሔር እንዲገፍላቸው እየተመኘሁ! በሀገራችን ውስጥ ዘላቂ ሰላም ፍትህ ነፃነት ና እኩልነት እንዲሰፍን ላማድረግ አንዲሁም በጭንቅ ውስጥ ያለውን ና ጥርቅም ብሎ ለመዘጋት የተቃረበውን የዲሞክራሲዊ ስርዓትን ና የፖለቲካ ምህዳር በሚፈለገው ደረጃ ለማስፋት የፖለቲካ ውሳኔ የሚያስፈልጋቸውን ጉዳዮች ልዩ ትኩረት በመስጠት አፋጣኝ ምላሽ እንዲሰጥ ኃላፊነት እንደሚሰማው አንድ ዜጋ ማሳሰብ እፈልጋለሁ!. እግዚአብሔር ኢትዮጴያን ይባርክ!
ዶ/ር ይህዓለም ታምሩ
አዲስ አበባ ኢትዮጰያ
ቀን 4/8/2018 ዓ.ም