Dr. Seid Arage

Dr. Seid Arage Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Dr. Seid Arage, Medical and health, Addis Ababa.

Maternal Fetal Medicine sub specialist
( በእናቶችና ጽንስ ህክምና አደጋ ላይ ወይም ውስብስብ ችግሮች ላይ ያተኮረ ከፍተኛ ህክምና )
ረዳት ፕሮፌሰር
አድስ አበባ ዩኒቨርሲቲ
በረካ የእናቶችና ህጻናት ማእከል
+ 251910161920

28/05/2026

አልሀምዱሊላህ፣ ዛሬ ሌላ የሕይወት ዓመትን በሰላም አጠናቅቄያለሁ። ወደ ኋላ ስመለስ፣ ያለፉት ዓመታት በፈተና፣ በትምህርት፣ በእምነት እና በአላህ ታላቅ በረከት የተሞሉ ነበሩ።

ወደ አዲሱ ምዕራፍ ስገባ፣ ጸሎቴ መጪው ጊዜ ይበልጥ አላማ ያለው፣ በሰላም፣ በእምነት እና በበረካ የተሞላ እንዲሆን ነው። አላህ እያንዳንዱን እርምጃዬን በሂክማ ፣ እያንዳንዱን ቀኔን በኸይር ፣ እና ለሌሎች ብርሃንና በረከት እንዲሆን እየተመኘሁ

ለመልካም ምኞታችሁ፣ ለዱዓችሁ ሁላችሁንም ከልብ አመሰግናለሁ። አላህ በሕይወታችሁ ሁሉ ላይ በረከቱንና ስኬቱን ያብዛላችሁ። አሚን።

22/05/2026

ከወሊድ በኋላ የሚከሰት ድብርት (Postpartum Depression)
በጊዜ መታወቅና መታከም ህይወትን ያድናል፤ ጤናዎንም ይጠብቃል። ማንኛውም አይነት ምልክት ከተሰማዎት ችላ አይበሉ፤ እርዳታ ለመጠየቅም ወደኋላ አይበሉ!
ጤናዎን ዘወትር ይከታተሉ!

11/05/2026

“በጥቁር አንበሳ ምን እየሰራህ ነው?” ብለው የሚጠይቁ ብዙ ጓደኞቼና ባልደረቦቼ አሉ።

በአሁኑ ጊዜ በTikur Anbessa Specialized Hospital የማህፀንና ፅንስ ሕክምና ክፍል ኃላፊ በመሆን እየሰራሁ ነው። ስራዬ የተለመደ ክሊኒካዊ አገልግሎትን ብቻ የሚያካትት ሳይሆን፣ እጅግ ውስብስብና ከፍተኛ ሀላፊነት ያላቸውን የእናቶችና የፅንስ ጤና ጉዳዮች መምራትን ያካትታል።

በተለይም፦

✅ ከፍተኛ ስጋት ያለባቸው እርግዝናዎችን መከታተል
✅ የፅንስ የደም ማነስ ሕክምና (Intrauterine Transfusion – IUT) የመሳሰሉ የላቀ የፅንስ ሕክምና ሂደቶችን መስራት
✅ ከመላ ሀገሪቱ የሚላኩ ውስብስብ የእናቶችና የፅንስ ደዌዎችን ህክምና
✅ የህክምና ተማሪዎችን፣ ሬዚደንቶችን፣ እና ሰብስፔሻሊቲ ተማሪዎችን ማስተማር
✅ የወደፊት ስፔሻሊስት ሐኪሞችን መገንባት
✅ የአካዳሚክና የክሊኒካል አገልግሎት ስርዓቶችን ማጠናከር

በተጨማሪም በBereka Mother and Child Center ልዩ የእናቶችና የፅንስ ሕክምና አገልግሎት እሰጣለሁ።

ለእኔ ሕክምና ማለት ሙያ ብቻ አይደለም፤
መሪነት ነው፣
ሀላፊነት ነው፣
አገልግሎት ነው፣
ትውልድ መገንባት ነው።

“እናቶችን መታደግ፣ ፅንሶችን መጠበቅ፣ የነገውን ስፔሻሊስቶች መገንባት።”

Medicine for me is not simply a profession — it is leadership, service, teaching, and responsibility.

Dr Seid Arage
Consultant Obstetrician and Gynecologist
Maternal Fetal Medicine subspecialist
Head department of Obstetrics and Gynecology AAU, CHS

Bereka Maternal and Child Health Specialty Center wishes you and your loved ones a blessed and joyful Eid. May your days...
20/03/2026

Bereka Maternal and Child Health Specialty Center wishes you and your loved ones a blessed and joyful Eid. May your days be filled with peace, health, and happiness.

عيد مبارك – كل عام وأنتم بخير، تقبل الله منا ومنكم.

ኢድ ሙባረክ

09/03/2026
18/02/2026

ነብሰ ጡር እናት ወይም አጥቢ እናት መጾም ትችላለች?
እንደሚታወቀው አንዲት እናት በእርግዝናዋ ጊዜ ወይም ጡት በምታጠባበት ወቅት ከመቼውም ጊዜ በላይ የተሻሉ እና በዛ ያሉ ምግቦችን መመገብ እና ፈሳሾችን ማብዛት ይጠበቅባታል። ከሌላው የእድሜ ክፍል በተለየ ሁኔታ የተመጣጠነ ምግብ የሰፈልጋታል ። ነፍሰ ጡር እናት ከሆነች ደሞ በተለየ ሁኔታ የመጀመሪያዎቹ 3 ወራት ላይ በተደጋጋሚ ማቅለሽለሽ እና ማስመለስ ስለሚያጋጥሟት በአንጻሩ ደግሞ በመጨረሻዎቹ ወራት ቶሎ የመጥገብ እና የምግብ ፍላጎት መቀነስ ስለሚከሰትባት በ24 ሰአት ዉስጥ ከ 5 ጊዜያት በላይ መመገብ ሊያስፈልጋት ይችላል።
ይህም በመሆኑ አንዲት ነብሰ ጡር ወይም አጥቢ እናት ለመጾም ከመነሳቷ በፊት ቀጥሎ ያሉትን ህክምናዊ ጉዳዮችን ማወቅና አስፈላጊውን ቅድመ ጥንቃቄ መውሰድ እንደሚገባት ለማስታወስ እንወዳለን ፦
በመጀመሪያዎቹ 3 ወራት የእርግዝና ጊዜ የሚገጥሙ ማስመለስ እና ማቅለሽለሽ ካለ በጾም እንደሚባባስ ማወቅ ያስፈልጋል
አንዲት ነብሰ ጡር ወይም አጥቢ እናት የስኳር በሽታ ካለባት ለእርሱም መድሃኒት የምትወስድ ከሆነ ጾም ላይ መጠንቀቅ ይገባታል
የደም ማነስ ፣ ተቅማጥ ፣ ደም ግፊት አንዲሁም ሌሎች ከእርግዝና ጋር ወይም ከ ማጥባት ጋር ተያይዘው የሚመጡ ተጨማሪ ህመሞች አለመኖራቸውን ማወቅ ይኖርባታል
በጾም ምታሳልፈው የቀኑ እርዝመት ከ 12 ሰአት እንዳይበልጥ ይመከራል
የአካባቢው የአየር ሁኔታ በጣም ሞቃታማ ከሆነ አለመጾሙ ይመከራል
ሱሁር መመገብ ፣ ጨው የበዛበትን መግብ መቀነስ ፣ በአንጻሩ ደሞ በተለይ ስሁር ላይ ፕሮቲን ፣ ፋይበር ነክ የሆኑ ጥሩ ምግቦችን መመገብና ፈሳሽ ነገሮችን በብዛት መውሰድ ይመከራል
ለመጾም ሲወስኑ ሃኪሞን ሳያማክሩ በአርግዝና ወቅት የሚሰጡ መድሀኒቶችን ማቁአረጥ እንደማይገባ ማወቅ ግድ ይላል
መንታ ወይም ከዚያም በላይ ጽንስ ካለ ከአምስት ወር በኀላ አለመጾሙ ይመከራል
አሁን ላይ የምጥ ሰሜቱ ካለም መጾም አይመከርም

ከላይ የተዘረዘሩትን ቅድም ጥንቃቄዎችን ያረገች እናት ረመዳኑአን በየትኛውም የእርግዝና እድሜ ላይ ብትጾም ፅንሱ ላይ ችግር እንደሌለው በርካታ ጥናቶች ይጠቁማሉ። ከዘጠኝ ወር ጊዜ ውስጥ አንድ ወር መፆም ጉዳት እንደሚያስከትል የሚአትት የጥናት ውጤት እንደሌለም ይታወቃል ። ሆኖም ግን እርግዝና ላይ ያለች እናት ከሚያስፈልጋት ጉልበት አኳያ ፆሙን ጀምራ ካልቻለች ወይም የድካም ስሜት ከተሰማት ቀጥሎም ራስ ምታት ከተሰማት በጾሙ መቀጠል አይገባትም። የመፆም ፍላጎቷ ካየለ ግን አንድ ቀን እየፆመችና አንድ ቀን እያፈጠረች አቅሟን እንድታይ ትመከራለች።
ፆመኛ የሆነች ነብሰ ጡር ወይም አጥቢ እናት እንዳትወስዳቸው የምትመከራቸው የምግብ አይነቶች
ጨው የበዛበት ምግብ ፣ ቅባትና ጮማ፣ ስኳር የበዛበት ምግብ
እንደማንኛውም ጊዜ ከሱስ ሁሉ መጠንቀቅ
ፆመኛ የሆነች ነብሰ ጡር ወይም አጥቢ እናት ( በተለይ ስሑር ላይ ) እንድተወስድ ምትመከራቸው የምግብ አይነቶች
በፕሮቲን የበለጸጉ የምግብ አይነቶችን ( ለምሳሌ ለውዝ ፣ ምስር፣ አተር ወይም የባቄላ ፉል
በፋይበር የበለጸጉ የምግብ አይነቶችን ( ለምሳሌ ተምር )
ፍራፍሬዎችን ( ለምሳሌ የማንጎ ፣ የአቮካዶ ፣ የፓፓዬ ፣ ወዘተ ጭማቂዎችን
ሆልግረይን ምግቦችን( ለምሳሌ የቂንጬ ሾርባ ፣ ውሃ በወተት )
በፆመ ላይ የሆነች ነብሰ ጡር ወይም አጥቢ እናት የሚከተሉትን ምልክቶች ካየች ሀኪሟን እንድታማክር ትጠየቃለች
የምጥ ምልክት
ረዘም ላለ ሰአት የልጅ እንቅስቃሴ መቀነስ
ከፍተኛ የሆነ ራስ ምታት ማጋጠም
ከፍተኛ የሆነ ድካም ፣ የውሃ ጥም ፣ ረሃብና ማዞር መከሰት
በጥቅሉ በጾሙ ምክንያት የሚመጣ ምልክቶችን መገምገም
በዶ/ር ሰይድ አራጌ
( የማህጸንና ፅንስ ስፔሻሊስት ሀኪም ፣ ረዳት ፕሮፌሰር ፣ ማተርናል ፌታል ሜድስን ሰብ ስፔሻሊስት በአዲስ አበባ ዩንቨርስቲ ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል እና በረካ የእናቶችና ህጻናት ህክምና ማዕከል )

አዲስ አበባ

With College of Health Sciences Addis Ababa University – I just got recognized as one of their top fans! 🎉
23/01/2026

With College of Health Sciences Addis Ababa University – I just got recognized as one of their top fans! 🎉

ሾተላይ እና ሳይንሳዊ መፍትሄው ጥንዶች አንድ ልጅ ብቻ ወልደው በቀጣይ የተወለደው ልጅ ሕይወት ሲያልፍ ወይም ሴቶች ለእርግዝና ሲቸገሩ በተለምዶ ሾተላይ አለባቸው ሲባል ይስተዋላል። ሾተላይ ተ...
18/01/2026

ሾተላይ እና ሳይንሳዊ መፍትሄው

ጥንዶች አንድ ልጅ ብቻ ወልደው በቀጣይ የተወለደው ልጅ ሕይወት ሲያልፍ ወይም ሴቶች ለእርግዝና ሲቸገሩ በተለምዶ ሾተላይ አለባቸው ሲባል ይስተዋላል። ሾተላይ ተብሎ የሚጠራው ችግር በሕክምና አር ኤች ፋክተር (RH factor) ወይም አር ኤች ኢንኮምፓቲቢሊቲ (RH incompatibility) የሚል ስያሜ እንዳለው በጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የፅንስ እና ማሕፀን ሕክምና ስፔሻሊስት እንዲሁም በማተርናል ፌታል ሜዲስን ሰብ ስፔሻሊስት ዶ/ር ሰኢድ አራጌ ይናገራሉ።

ሾተላይ (RH incompatibility) ሕመም

በጽንስ ጊዜ የሚከሰት ሾተላይ ተፈጠረ የሚባለው አባት ፖዘቲቭ፣ እናት ኔጌቲቭና ልጅ የአባቱን የደም አይነት ወስዶ ፖዘቲቭ በሚሆንበት ወቅት ብቻ ነው። እናት አር ኤች ፋክተር ሳይኖራት (ኔጌቲቭ ሆና) ፅንስ አርኤች ፋክተር ሲኖረው (ፖዘቲቭ ሲሆን) የእናት የበሽታ መከላከያ ስርዓት የፅንሱን አርኤች እንደባዕድ ይቆጥረዋል ይላሉ ዶ/ር ሰኢድ።

ቀጥሎም መከላከያ በማመንጨት ፅንሱ ላይ ችግር ይፈጠራል። የተፀነሰው ልጅ ለዚህ ችግር ይበልጥ ተጋላጭ የሚሆነው ከ28 ሳምንት የእርግዝና ጊዜ በኋላ (ሊወለድ በተቃረበበት) ነው። በደማቸው ውስጥ አር ኤች ፋክተር የሌላቸው ማለትም የደም አይነታቸው ኤ ኔጌቲቭ፣ ቢ ኔጌቲቭ፣ ኤቢ ኔጌቲቭ እና ኦ ኔጌቲቭ የሆኑ ሴቶች የደም አይነቱ ፖዘቲቭ (positive) ከሆነ ወንድ ሲፀንሱ እንዲሁም የፀነሱት ልጅ የደም አይነት ፖዘቲቭ (የአባቱን ሲይዝ) አር ኤች ፋክተር ወይም ኢንኮምፓቲቢሊቲ ተፈጠረ ይባላል።

አባት ፖዝቲቭ፤ እናት ኔጌቲቭ ሆኖ ፅንሱ ኔጌቲቭ የሚሆንበት (የእናቱን የሚይዝበት) አጋጣሚ ምንም ችግር አይፈጥርም ይላሉ ዶ/ር ሰኢድ።
የሰው ልጅ ባጠቃላይ ስምንት ዓይነት የደም አይነት ሲኖረው፤ አራቱ አር ኤች ፖዘቲቭ፤ አራቱ ደግሞ አር ኤች ኔጌቲቭ ናቸው። ትልቁ ጉዳይ የሚመጣው እናትየዋ በተፈጥሮዋ አር ኤች ኔጌቲቭ የሆነች እለት ነው።
የሚወለደው ልጅ የአባቱን ከያዘ ለናትየዋ የደም አይነት አዲስ እንግዳ ይሆናል። የልጁ የደም ዓይነት ሳይወለድ በማሕጸን ውስጥ እያለ ወይንም በወሊድ ሰዓት ከልጁ ደም ወደ እናትየዋ ይደማል (ይቀላቀላል)። በሚቀላቀልበት ጊዜ ደግሞ የልጁን የደም ዓይነት የናትየዋ የደም ዓይነት ስለማያውቀው እንደ በሽታ ይቆጥረዋል። ስለሆነም በመጀመሪያ እርግዝና ላይ በሽታ ብሎ ይመዘግበዋል።

እንደገናም እናት እርግዝና ስትይዝ ያንን የደም አይነት ቀጣይ ላይ በእርግዝና ከያዘች መጀመሪያ ላይ በሽታ ተብሎ የተመዘገበ ልጅ ስለሆነ የእናትየዋ የበሽታ መከላከያ ስርዓት ያን ልጅ ያጠፋቸዋል። ሳይወለድ ካጠፋቸው ልጁ ውስጥ እያለ የደም ማነስ ይኖረዋል። እድሉን አግኝቶ መወለድ ከቻለ እና ደም ማነስ ካልገጠመው ቢጫ ሆኖ እንዲወለድና አደጋ ውስጥ እንዲገባ ያደርገዋል።

በመጀመሪያ እርግዝና ወቅት ሾተላይ የማጋጠም እድል አነስተኛ ነው። ይህ ችግር በይበልጥ የሚስተዋለው 2ኛ እና ከዛ በላይ በሆነ ፅንስ ላይ ነው። የመጀመሪያ ፅንስ ላይ የእናት የመከላከያ ስርዓት እንደ በሽታ የቆጠረውን የጽንስ የደም አይነት የሚለይበት የሚሰጥበት በመሆኑ ነው።

ነገር ግን የመጀመሪያ እርግዝና ሲባል ከዚህ ቀደም ፅንስ ማቋረጥ እና መሰል ችግር ያላጋጠማት (እርግዝና ሙሉ በሙሉ ተፈጥሮ የማያውቅ) መሆን አለበት። ከዚህ ቀደም እናት ባላወቀችበት መንገድ እርግዝና ተፈጥሮ የነበረ ሊሆን ይችላል። ስለሆነም የመጀመሪያ እርግዝና በእርግጠኝነት ላይታወቅ ስለሚችል እንዲሁም በቀጣይ (2ኛ) እርግዝና ላይ የሚያስከትለውን ችግር ለመከላከል ሕክምና መሰጠት የሚጀምረው በመጀመሪያ እርግዝና ወቅት ነው።

አርኤች ፋክተር (ሾተላይ) የሚያስከትለው ችግር ፅንሱ ሆድ ውስጥ እያለ የደም ማነስ ማጋጠም፣ ፅንስ መቋረጥ፣ ወቅቱ ሳይደርስ መወለድ፣ ከተወለደ በኋላ የደም ማነስ ችግር፣ የተወለደ ልጅ ቢጫ መሆን፣ ሾተላይ እና ሳይንሳዊ መፍትሄው የተወለደ ልጅ ላይ የአእምሮ ችግርና ልጅ ከተወለደ በኋላ ሕይወት ማጣት ናቸው።

መረጃዎች እንደሚያሳዩት በዓለም አቀፍ ደረጃ እንደየ ሀገሩ የተለያየ ቢሆንም የደም አይነታቸው ፖዘቲቭ ማለትም አር ኤች ፋክተር ያላቸው ሰዎች ብዛት ኔጌቲቭ የደም አይነት ካላቸው ሰዎች አንፃር ከፍተኛ ነው። እንደ ዶክተር ሰኢድ ንግግር፤ የአር ኤች ፋክተር ችግር በመቶኛ ሲቀመጥ ከ100 ሰዎች መካከል በ16 ላይ ያጋጥማል። የቅርብ ጥናት ባይኖርም በኢትዮጵያ ከ100 ሰዎች ምናልባት ከስድስት እስከ አስር በመቶ ሰው ላይ ይከሰታል።

ስለሆነም ኔጌቲቭ የሆነች (አር ኤች ፋክተር የሌላት) እና ፖዘቲቭ አር ኤች ካለው የፀነሰች ነፍሰ ጡር ሴት 28ኛ ሳምንት ላይ ሕክምና ይሰጣታል። ይህም ጽንሱ ፖዘቲቭ ከሆነ ችግር አንዳይፈጠር ያደርጋል። ኔጌቲቭ ከሆነ ደግሞ ጥቅም ባይኖረውም ጉዳት አያስከትልም።
ይህ ሕክምና ምንም አይነት ተጓዳኝ ችግር ስለማያስከትል ተጋላጭ ለሆኑ እናቶች በሙሉ እንዲሰጥ ይደረጋል።

አንዲት ሴት ይህ ችግር አጋጥሟታል የሚባለው የአባት የደም አይነት ፖዘቲቭ (አር ኤች ፋክተር ያለው)፣ የእናት ኔጌቲቭ (አር ኤች ፋክተር የሌለው) እና የተፀነሰው ልጅ ፖዘቲቭ (አር ኤች ፋክተር ያለው) ሲሆን ነው።

የአባት የደም አይነት ፖዘቲቭ ቢሆንም 40 በመቶ የሚሆነው ፅንስ የእናትን የደም አይነት ኔጌቲቭ ስለሚይዝ ችግር አያጋጥመውም። በተመሳሳይ የጥንዶቹ (የሁለቱም) የደም አይነት ኔጌቲቭ ከሆነ የሚፀነሰው ልጅም ኔጌቲቭ ስለሚሆን የሾተላይ ችግር አይፈጠርም።

ከዚህ ቀደም የሾተላይ ችግር ያጋጠማቸው ጥንዶች በቀጣይ እርግዝና ላይ ፅንሱ የእናትን የደም አይነት (ኔጋቲቭ) የመያዝ እድል ሊኖረው ይችላል። ነገር ግን ፅንሱ በድጋሚ የአባቱን የደም አይነት ከያዘ ሕክምና እንዲያገኝ ይደረጋል። አር ኤች ኢንኮፓቲቢሊቲ (ሾተላይ)ና ሕክምናው
በጥቅሉ ከዚህ ቀደም የሾተላይ ችግር ያጋጠማቸው እናቶች በቀጣይ እርግዝና ለችግሩ ተጋላጭ መሆን ወይም አለመሆናቸውን ለማወቅ የሚደረግ የላብራቶሪ ምርመራ፣ 28ኛ የእርግዝና ሳምንት ላይ የሚሰጥ መድሃኒት፣ ከወሊድ በኋላ የሚሰጥ መድሃኒት፣ ፅንስ ሆድ ውስጥ እያለ ደም እንዲሰጠው ማድረግና ልጅ ከተወለደ በኋላ የሚሰጥ ሕክምና ይጠቀሳሉ።

ሾተላይ /አር ኤች ኔጋቲቭ (RH-)/ ችግርን መከላከል ይቻላል። 28ኛ ሳምንት ላይ ሲደርሱ ወይንም ሰባት ወር መግቢያ ላይ ሲደረስ የዚህን በሽታ መከላከያ መርፌ መወጋት ይቻላል። ይህ በቂ አይደለም። ዋናው ተከላካይ እናት እንደወለደች በሰዓታት ውስጥ የልጁ የደም ዓይነት ይታይና የእናትየውን ከመሰለ ይቀራል፣ የአባትየውን ከመሰለና ከታወቀ ድጋሚ ያንኑ መድሃኒት ሁለተኛ ዙር መድሃኒቱን እንዲወስድ ይደረጋል።

በሽታ የሚባለውም ይህንን እድል ያላገኙ እናቶች ላይ ነው። በኢትዮጵያ ይህ መድሃኒት በጣም ውድ ከመሆኑም ባሻገር በቀላሉ ላይገኝ ይችላል። ይህ ሆኖም አልፎም አንዳንድ ሰዎች መድሃኒቱንም ወስደው ውስን ሰዎች ለዚህ ችግር ይጋለጣሉ።

ብዙ ጊዜ ችግር ላይ የሚወድቁት ግን መድሃኒቱን ያላገኙት፣ በክትትላቸውም ያንን እድል ማግኘት ያልቻሉ ሰዎች ናቸው። መድሃኒቱ ማቀዝቀዣ የሚፈልግ በመሆኑ ከቦታ ቦታ ሲንቀሳቀስ ለጸሃይ ከተጋለጠ አያገለግልም። እንደገናም ሀገር ውስጥ የሚመረት መድሃኒት ባለመሆኑና ከውጭ ሀገር ስለሚመጣ በተለያየ መንገድ አላግባብ የሚመጣባቸው ሁኔታዎች ስለሚኖሩ መድሃኒቱ ውጤታማ ያለመሆን ባህሪም ሊኖረው ይችላል።

ሾተላይ ያጋጠማቸውን እናቶች በማዕከሉ እርግዝናቸውን ካወቁ አራት ወራት ጀምሮ ክትትል ይደረግላቸዋል። ደም ካነሳቸው ደም ይሰጣቸዋል። ለቢጫነት የሚጋለጡ ሆነው ከተገኙ ደግሞ ከተወለዱ በኋላ በሆስፒታሉ ውስጥ ባለ ጽኑ ሕሙማን ክፍል ውስጥ ለዚሁ ተብሎ በተመደቡ ባለሙያዎች የሾተላይ ሕክምና ይደረግላቸዋል።

የሾተላይ ሕመም ጽንሱ ላይ ይታወቃል። የመጀመሪያው የልየታ መንገድ እናትየዋ /አር ኤች ኔጋቲቭ (RH-)/ መሆኗ ነው። ይህንን ተከትሎ የላቦራቶሪ ምርመራ ከእናትየው ደም ተወስዶ በሚደረገው ምርመራም ውጤቱ ጥቆማ ይሰጣል።

የደም ማነስ መኖርና አለመኖሩን ለማወቅ ሙያዊ ሥራ ይሠራል። ሥራውም የሚሠራው በአልትራ ሳውንድ ነው። ዘመናዊ ቴክኖሎጂን በመጠቀም ከቀድሞው በተሻለ እና በቀላል መንገድ የልጅን የጭንቅላቱን የአእምሮ ክፍል በአልትራ ሳውንድ በማየት ደም ማነስ እንዳለበት እና እንደሌለበት ማወቅ ይቻላል።

አንዲት እናት ሳታውቅ እንኳን እርግዝና ብትይዝ ሾተላይ ያለበት ሰው ልጅ አይወልድም የሚለውን አባባል ማስቀረት ያስፈልጋል። በሆስፒታሉን ወደፊት ከተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት ሪፈራል በመቀበል ማከም እንፈልጋለን። ለዚህም ብቁ የሰው ኃይል እና የሕክምና መሳሪያዎች አሉ። መማር ማስተማሩም ይህንን ተግባር ማስፋፋት ዓላማ ማድረጉን ይጠቁማሉ።

እስካሁን ባሉ ጥናቶች ደሙን ወስደው ካደጉ በኋላ የተሰሙ ችግሮች የሉም። በርግጥ ሳይንሱ ለሌላውም ዓለም አዲስ ነው። ነገር ግን በተሻለ ሁኔታ ርቀው ሄደዋል። ተሞክሮ ያለው ባለፉት ከስምንት እስከ 10 ዓመታት ውስጥ ነው። የእስካሁንን በመሰብሰብ ጥናት ውስጥ እናስገባለን።

ፅንስ ሆድ ውስጥ እያለ የደም ማነስ ሲያጋጥመው ደም እንዲሰጠው ይደረጋል። ይህም የደም አይነታቸው ኔጊቲቭ (አር ኤች ፋክተር ከሌላቸው) ሰዎች የተወሰደ ነው። በይበልጥ ኦ ኔጌቲቭ የደም አይነት ለፅንሱ እንዲሰጥ ይደረጋል።

ስለሆነም የፅንሱና የእናት የደም አይነት ኔጌቲቭ (ተመሳሳይ) እንዲሆን ማድረግ ችግሩን ያስተካክላል። እናት ኔጌቲቭ እና አባት ፖዝቲቭ የደም አይነት ላለው ፅንስ በሙሉ 28ኛ የእርግዝና ሳምንት ላይ ሕክምና ይሰጣል። ነገር ግን በዚህ ወቅት የሚሰጥ ሕክምና በድጋሚ ከወሊድ በኋላ እንዲሰጥ የሚደረገው ፅንሱ ከተወለደ በኋላ ፖዝቲቭ የደም አይነት እንዳለው ሲረጋገጥ ነው።

ከእናቱ ጋር በተመሳሳይ መልኩ ኔጌቲቭ ከሆነ ሕክምና (መድሃኒት) አያስፈልገውም። ፅንስ ሆድ ውስጥ እያለ የደም አይነቱን ማወቅ ይቻላል። ነገር ግን የደም አይነቱን ለማወቅ በሚደረግ ምርመራ ችግሩን ላለማባባስ ሲባል በ28ኛ የእርግዝና ሳምንት ላይ ተጋላጭ ለሆኑ እናቶች በሙሉ ሕክምናውን መስጠት ተመራጭ ተደርጓል። ፅንስ ሲቋረጥ ወይም ልጅ ሕይወቱን ሲያጣ ከአር ኤች ችግር ጋር የማማያዝ ሁኔታዎች አሉ።
አር ኤች ኔጌቲቭ ወይም ፖዘቲቭ የሆኑ እናቶች በእርግዝና ወቅት በተለያየ በሽታ (ችግር) ምክንያት ልጅ ሊያጡ ይችላሉ። ነገር ግን ከአር ኤች ፋክተር (የሾተላይ ችግር) ጋር ሊያያዝ እንደማይገባው ያመለክታሉ።

በሾተላይ ላይ ያለው የተሳሳተ ግንዛቤ የእናቶችን ትክክለኛ ችግር እንዳይታወቅ በማድረግ አስፈላጊውን ሕክምና እናዳያገኙ ያደርጋል። እንደገናም የስነልቦና ችግር በማስከተል በቀጣይ እርግዝና ላይ ጫና ያስከትላል።

አር ኤች ኔጌቲቭ የሆኑ ሰዎች ጤናማ ናቸው። ተጋላጭ የሆኑ ሴቶች ችግሩን አስቀድሞ በመከላከል እና በሕክምና መውለድ ይችላሉ።
የአር ኤች ፋክተር ችግር (ሾተላይ) መከላከያ መንገድ
ትዳር ሲመሰረት የአር ኤች ፋክተር ምርመራ ማድረግ፣ ኔጌቲቭ የደም አይነት ያላቸው ሰዎች ደም ቢለግሱ፣ ተጋላጭ የሆኑ እናቶች በማንኛውም ችግር ፅንስ መቋረጥ ሲያጋጥማቸው ሕክምና ማድረግ (መድሃኒት መውሰድ) መፍትሄ መሆኑንም ይጠቅሳሉ።

አር ኤች ኔጋቲቭ ሆነው እርግዝና ያላቸው ክትባቱን ለማግኘት በ28 ኛ ሳምንት እና ከወሊድ በኋላ መውሰድ አለባቸው። ገንዘብ ቢጎድል እንኳን ከወሊድ በኋላ ወዲያውኑ ሲወለድ የሚወሰደውን መውሰድ ያስፈልጋል።
በእርግዝና ጊዜ የሾተላይ በሽታ ያለባቸው እናቶች ልክ እንደማንኛውም እርግዝና በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል በብቁ ባለሙያዎች በነጻ ሕክምና ያገኛሉ። የሕክምና ባለሙያዎች ችግሩ የተባባሰ ደረጃ ላይ ሳይደርስ ወደ ሆስፒታሉ ታካሚዎችን ቢልኩ ሆስፒታሉ ለማከም ዝግጁ ነው።

14/01/2026

Address

Addis Ababa
7080

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Dr. Seid Arage posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share