Hakim

Hakim Ethiopian blend of medicine, history & humor.
(241)

በቅዱስ ጴጥሮስ ሆስፒታል ዛሬ ለህክምና የመጡ ተገልጋይ በወቅቱ ይዘውት የነበረውን 16,000 ብር ይጥላሉ ፣ ይህንንም ገንዘብ ያገኙት ባለሞያዎች ገንዘቡን በማስቀመጥ ተገልጋዩን በመፈለግ ይህ...
11/08/2026

በቅዱስ ጴጥሮስ ሆስፒታል ዛሬ ለህክምና የመጡ ተገልጋይ በወቅቱ ይዘውት የነበረውን 16,000 ብር ይጥላሉ ፣ ይህንንም ገንዘብ ያገኙት ባለሞያዎች ገንዘቡን በማስቀመጥ ተገልጋዩን በመፈለግ ይህንን ገንዘብ ለባለቤቱ መልሰዋል። በዚህም ተገልጋዩ ለባለሞያዎቹና ለተቋሙ ያላቸን ምስጋናና ክብር አቅርበዋል።

የሆስፒታሉ ስራ አስኪያጅ ዶ/ር አብርሀም እሸቱ ይህንን መልካም ተግባር የፈፀሙትን የላብራቶሪ ክፍል ባለሞያዎች
- ነፃነት ጉታ
- ሁንዳኦል ጫላ
- ተመስገን ባሳዝነው
- ሳሙኤል አንዳርጌ
በመጥቀስ "እናንተ እውነተኛ የሆስፒታላችን ጀግኖች ላሳያችሁት ሞያዊ እና ስነምግባራዊ ከፍታ ሆስፒታሉ ያመሰግናችኋል!" በማለት ምስጋና አቅርበዋል::

Telegram: t.me/HakimEthio

ያለ ሐኪም ማዘዣ ወረቀት ስለሚገዙ መድኃኒቶችOTC (Over-the-Counter) መድኃኒቶች ማለት ያለ ሐኪም ማዘዣ ወራቀት (Presecription) የሚገዛ/የሚሰጥ ማለት እንጂ ያለ ባለሙያ ...
11/08/2026

ያለ ሐኪም ማዘዣ ወረቀት ስለሚገዙ መድኃኒቶች

OTC (Over-the-Counter) መድኃኒቶች ማለት ያለ ሐኪም ማዘዣ ወራቀት (Presecription) የሚገዛ/የሚሰጥ ማለት እንጂ ያለ ባለሙያ ምክር የሚወሰድ/የሚሰጥ ማለት አይደለም!

በማህበረሰባችን ውስጥ “ያለ ማዘዣ (OTC)” የሚሸጡ መድኃኒቶችን በተመለከተ ትልቅ የአስተሳሰብ ክፍተት አለ። ብዙዎቻችን እነዚህ መድኃኒቶች ከፋርማሲ ለመግዛት የሐኪም ወረቀት (Prescription) ስላላስፈለጋቸው ብቻ “ያለ ምንም የጤና ባለሙያ ክትትልና ምክር በፈለግነው መንገድና በፈለግነው ግዜ መውሰድ እንችላለን” ብለን እናስባለን።

ነገር ግን እውነታው ይህ አይደለም! OTC ማለት ያለ ማዘዣ ወረቀት (Presecription) የሚገዛ (Over-the-Counter) ማለት እንጂ ያለ ባለሙያ ምክር (without consultation with Health profession) በራስ ፈቃድ የሚወሰድ ማለት አይደለም።

መድኃኒትነታቸው እስከተረጋገጠ ድረስ፣ እያንዳንዱ የ OTC መድኃኒት የራሱ የሆነ የጎንዮሽ ጉዳት፣ የመጠን (Dose) ገደብ እና ከሌሎች መድኃኒቶችና ምግብ ጋር የመጋጨት (Drug-Drug, Drug-food Interaction) ባህሪ አለው።

የOTC መድኃኒቶችን ያለ ሕክምና ባለሙያ ምክር ለምን መውሰድ የለብንም? የሚከተሉትን ነጥቦች/የጉዳት ማሳያዎችን ልብ እንበል:

1. “ደህንነቱ የተጠበቀ ነው” የሚባለው ፓራሲታሞል (Paracetamol/Acetaminophen) የሚያደርሰው የጉበት አደጋ

በብዛት ያለ ማዘዣ ከሚወሰዱ መድኃኒቶች ቀዳሚውን ስፍራ የሚይዘው ፓራሲታሞል ነው። ሰዎች ለራስ ምታት፣ ለትኩሳትና ለተለያዩ ህመሞች ያለ ገደብ ሲወስዱት ይታያል።

ነገር ግን British Journal of Clinical Pharmacology ላይ የወጣ ጥናት እንደሚያሳየው፣ በአውሮፓና በአሜሪካ ለድንገተኛ የጉበት ጉዳት (Acute Liver Failure) ዋነኛው ምክንያት ያለ ሐኪም ወይም ፋርማሲስት ምክር የሚወሰድ የፓራሲታሞል መጠን ማለፍ (Accidental Overdose) ነው። በተለይ ሰዎች ከተለያዩ የጉንፋን መድኃኒቶች ጋር ደባልቀው ሲወስዱ ሳያውቁት መጠኑን ከተፈቀደው በላይ ይጨምራሉ። ይሄም ለከፍተኛ ጉዳት ሊዳርጋቸው ይችላል፡፡

2. የህመም ማስታገሻዎች (NSAIDs) እና የጨጓራ ደም መፍሰስ እንዲሁም የኩላሊት ጉዳት

እንደ አይቡፕሮፌን (Ibuprofen)፣ ዲክሎፌናክ (Diclofenac) እና አስፕሪን (Aspirin) ያሉ የህመም ማስታገሻዎች በየትኛውም ፋርማሲ ያለ ማዘዣ ይገኛሉ።

The Lancet የተባለው ታዋቂ የሕክምና መጽሔት(journal) ባወጣው መጠነ-ሰፊ ጥናት (Meta-analysis) መሠረት፣ እነዚህን መድኃኒቶች ያለ ባለሙያ ምክርና ክትትል ለረጅም ጊዜ መውሰድ የጨጓራ መቁሰልና ከባድ የውስጥ ደም መፍሰስ (Gastrointestinal Bleeding) አደጋን በሦስት እጥፍ ይጨምራል። ከዚህም በተጨማሪ የኩላሊት የደም ዝውውርን በመቀነስ ለዘላቂ የኩላሊት መታወክ (Chronic Kidney Disease) ያጋልጣሉ።

3. የልብና የደም ግፊት ህመምተኞች ላይ የሚፈጠር ድንገተኛ አደጋ

ብዙ ለጉንፋን ማስታገሻነት ጥቅም ላይ ከሚዉሉ መድኃኒቶች ውስጥ Decongestants (ለምሳሌ Pseudoephedrine ወይም Phenylephrine) የሚባሉ ንጥረ ነገሮች በዉስጣቸው የያዙ መድኃኒቶች ዋነኛዎች ናቸው። እነዚህ መድኃኒቶች እንደ የአፍንጫ መታፈን ያሉ ምልክቶችን የሚቀንሱ ብሆኑም፣ የደም ሥሮችን የማጥበብ ባህሪ አላቸው። በዚህ ምክንያት ደግሞ ድንገተኛ የደም ግፊት መጨመርና ሌሎች አደጋዎችን ሊያስከትል ይችላል፡፡

በተለያዩ ጆርናሎች ላይ የወጡ ጥናቶች እንደሚያስጠነቅቁት ፣ የደም ግፊት ወይም የልብ ሕመም ያለባቸው ሰዎች እነዚህን የ OTC የጉንፋን መድኃኒቶች ያለ ጤና ባለሙያ አማካሪነት ሲወስዱ፣ ድንገተኛ የደም ግፊት መጨመር (Hypertensive Emergency/Crisis) በዚህም ምክንያት ለስትሮክ (Stroke) የመጋለጥ ዕድላቸው በከፍተኛ ሁኔታ ይጨምራል።

4. መድኃኒት ከመድኃኒት ጋር መጋጨት (Drug-Drug Interactions)

አንድ ሰው ለሌላ ሥር የሰደደ ሕመም (Chronic disease) (ለምሳሌ ለስኳር፣ ለግፊት ወይም ለደም ማቅጠኛ) መድኃኒት እየወሰደ ሊሆን ይችላል። የጤና ባለሙያን ሳያማክሩ የሚወሰዱ የ OTC መድኃኒቶች ከፍተኛና አደገኛ መስተጋብር ሊፈጥሩ ይችላሉ።

◆ ምሳሌ፦ የደም ማቅጠኛ/Anti-Coagulant (Warfarin) የሚወስድ ሰው፣ ከሐኪም ጋር ሳይመካከር በራሱ ውሳኔ/ፈቃድ ብቻ አስፕሪን ወይም አይቡፕሮፌን ቢወስድ፣ የደሙ መቅጠን መጠን ከቁጥጥር ውጪ ሆኖ ለሞት የሚያደርስ የውስጥ ደም መፍሰስ ሊያስከትል ይችላል።

💡 እናሳ? እናማ

◆ እነዚህንና መሰል ችግሮችን ለመቅረፍ መድኃኒት ሰጪውም ገዢውም በቂ መረጃ መለዋወጥ አለባቸው።

◆ መድኃኒት ምግብ አይደለም! “ያለ ማዘዣ ይሸጣል” ማለት “ፈጽሞ አይጎዳም” ማለት አይደለም።

◆ ማንኛውንም የOTC መድኃኒት ከመግዛታችን እና ከመውሰዳችን በፊት ሐኪሞችን ወይም በፋርማሲ ውስጥ የሚገኙትን የመድኃኒት ባለሙያዎች (Pharmacists) ማማከር ፍጹም አማራጭ የሌለው ተግባር ነው።

ባለሙያው፦
◆ መድኃኒቱ ለእርስዎ ትክክለኛ መሆኑን፣
◆ መወሰድ ያለበትን ትክክለኛ መጠን (Dose) እና የሰዓት ልዩነት፣
◆ ከሌሎች የሚወስዷቸው መድኃኒቶች ጋር (ባሕላዊ መድኃኒቶችን ጨምሮ) የመጋጨት ዕድል እንዳለው እና እንደሌለው ያረጋግጥልዎታል።

“ጤናችንን በግምት ላይ አንጣል፤ ያለ ማዘዣ የሚገዙ መድኃኒቶችንም ቢሆን በባለሙያ ምክርና መመሪያ ብቻ እንጠቀም!”

References

1. EFDA. Over-the-Counter Medicines Lists for Ethiopia. Third Edition (July 2022)

2. Craig DG, Bates CM, Davidson JS, Martin KG, Hayes PC, Simpson KJ. Overdose pattern and outcome in paracetamol‐induced acute severe hepatotoxicity. British journal of clinical pharmacology. 2011 Feb;71(2):273-82.

3. Larson AM, Polson J, Fontana RJ, Davern TJ, Lalani E, Hynan LS, Reisch JS, Schiødt FV, Ostapowicz G, Shakil AO, Lee WM; Acute Liver Failure Study Group. Acetaminophen-induced acute liver failure: results of a United States multicenter, prospective study. Hepatology. 2005 Dec;42(6):1364-72. doi: 10.1002/hep.20948. PMID: 16317692.

4. Craig DG, Bates CM, Davidson JS, Martin KG, Hayes PC, Simpson KJ. Staggered overdose pattern and delay to hospital presentation are associated with adverse outcomes following paracetamol-induced hepatotoxicity. Br J Clin Pharmacol. 2012 Feb;73(2):285-94. doi: 10.1111/j.1365-2125.2011.04067.x. PMID: 22106945; PMCID: PMC3269587.

5. Bhala, N., et al. "Vascular and upper gastrointestinal effects of non-steroidal anti-inflammatory drugs: meta-analyses of individual participant data from randomised trials." Lancet (London, England) 382.9894 (2013): 769-779.

6. Zhang X, Donnan PT, Bell S, Guthrie B. Non-steroidal anti-inflammatory drug induced acute kidney injury in the community dwelling general population and people with chronic kidney disease: systematic review and meta-analysis. BMC Nephrol. 2017 Aug 1;18(1):256. doi: 10.1186/s12882-017-0673-8. PMID: 28764659; PMCID: PMC5540416.

7. Brett, Allan S. "Effect of Pseudoephedrine on Blood Pressure and Heart Rate." NEJM Journal Watch (2005): JC200509090000006.

8. Kernan, Walter N., et al. "Phenylpropanolamine and the risk of hemorrhagic stroke." New England Journal of Medicine 343.25 (2000): 1826-1832.

9. Whelton, Paul K., et al. "2017 ACC/AHA/AAPA/ABC/ACPM/AGS/APhA/ASH/ASPC/NMA/PCNA guideline for the prevention, detection, evaluation, and management of high blood pressure in adults: a report of the American College of Cardiology/American Heart Association Task Force on Clinical Practice Guidelines." Journal of the American College of Cardiology 71.19 (2018): e127-e248.

10. Chan TY. Adverse interactions between warfarin and nonsteroidal antiinflammatory drugs: mechanisms, clinical significance, and avoidance. Ann Pharmacother. 1995 Dec;29(12):1274-83. doi: 10.1177/106002809502901214. PMID: 8672833.

Elias Mohammed (B.Pharm, MSc in Clinical Pharmacy)
Hiwot Fana Comprehensive Specialized Hospital
Haramaya University

Telegram: t.me/HakimEthio

🔆Ethio Tebib Hospital was proud to sponsor the 12th Annual Conference of the Ethiopian Gastroenterology Association (EGA...
11/08/2026

🔆Ethio Tebib Hospital was proud to sponsor the 12th Annual Conference of the Ethiopian Gastroenterology Association (EGA) on August 1, 2026, held under the theme “Bridging Research and Evidence-Based Medicine with Clinical Practice in Gastroenterology.”

The conference brought together healthcare professionals to explore advances in gastroenterology, including luminal imaging, medical AI, and precision approaches for early detection of mucosal and bowel diseases.

An important interdisciplinary session focused on pancreatic and hepato-pancreato-biliary (HPB) malignancies, highlighting modern approaches to oncology, neoadjuvant therapy, and complex surgical management.

Discussions also covered inflammatory bowel disease (IBD), including post-surgical care, dietary management, and challenges in biologic therapy within resource-limited settings.

Through our sponsorship, Ethio Tebib Hospital is proud to support initiatives that bring healthcare professionals together, foster the exchange of knowledge and expertise, and contribute to the continued advancement of healthcare in Ethiopia.

📞For more information and to schedule an appointment, call +251933745555 or call our toll-free number 9000.

📍Our address is located on the road leading to Kolfe, Masalemiya Sefereselam.

📱Telegram 📱Tiktok 📱Facebook 📱Instagram 📱Youtube

𝐄𝐭𝐡𝐢𝐨-𝐓𝐄𝐁𝐈𝐁 𝐇𝐨𝐬𝐩𝐢𝐭𝐚𝐥
We strive for your health!!

🔴 እርግዝና ከሚጠበቀው 40 ሳምንት በላይ ሲዘገይ 👉 ብዙ ነፍሰጡር እናቶች ከ 37-40 ሳምንታት መካከል ባለው ጊዜ  ይወልዳሉ።👉 ሆኖም ከ5-10% የሚሆኑት ሴቶች እስከ 42 ሳምንት እርግዝ...
11/08/2026

🔴 እርግዝና ከሚጠበቀው 40 ሳምንት በላይ ሲዘገይ

👉 ብዙ ነፍሰጡር እናቶች ከ 37-40 ሳምንታት መካከል ባለው ጊዜ ይወልዳሉ።

👉 ሆኖም ከ5-10% የሚሆኑት ሴቶች እስከ 42 ሳምንት እርግዝናቸው ይቀጥላል፤ ይህም ቀኑ ያለፈ እርግዝና ብለን እንጠራዋለን።

🔴 ስለእነዚህ የእርግዝና ጊዜ ማወቅ አስፈላጊ የሆነው ለምንድን ነው?

👉 የፅንስ የምግብ እና ኦክስጅን ምንጭ የሆነው የእንግዴ ልጅ ተግባር ከ 41-42 ሳምንታት በኋላ ማሽቆልቆል ይጀምራል።

👉 የእንሽርት ውሃ ፈሳሽ መጠን መቀነስ ይጨምራል ይህም ፅንስ እትብት ላይ ጫና መፍጠር ይጀምራል።

👉 የፅንስ ሆድ ውስጥ እያለ ሞት ቀስ በቀስ ከ41 ሳምንት በኃላ ይጨምራል፤ ይሄውም ከ1 -2 የሚሆን የፅንስ ሞት 40 ሳምንት ላይ ከ1000 እርግዝና የሚከሰት ሲሆን ከ41 ሳምንት በኃላ ወደ 2-3 ከ1000 እርግዝናዎች ከፍ ይላል።

👉 የፅንስ ኪሎ መጨመር እና በወሊድ ጊዜ የትከሻ ከማህፀን በቀላሉ አለመውጣት አደጋን መጨመር እና በኦፕሬሽን የመውለድ እድል ከፍ እንዲል ያደርጋል።

🔴 ከ40 ሳምንት በኃላ ስላለ እርግዝና ምን ይመከራል?

💥 ምንጭ 👉አብዛኛው አለም የተስማማባቸው የማህፀን እና ፅንስ ህክምና መመሪያዎች (ACOG እና RCOG)

👉 በየሳምንቱ ወይም በሳምንት ሁለት ጊዜ የአልትራሳውንድ ክትትል ማድረግ

1. የምጥ መርፌ በመስጠት እንዲወልዱ የሚመከርበት ጊዜ

👉 ከ41+0 -42+0 ሳምንት ላይ እንዲሰጥ ይመከራል ፤ ይህም የፅንስ ሆድ ውስጥ ሞትን የሚቀንስ ሲሆን በጥናቶች በኦፕሬሽን የመውለድ እድልን በተጋነነ ደረጃም አይጨምርም።

2. ምጥ በራሱ እስከሚጀምር መጠበቅ

👉 በቂ ክትትል እየተደረገ ፣ክትትል ላይ የፅንስ ጤናማነትን በበቂ ሁኔታ ከተረጋገጠ ምጥ መጠበቅ እንደአማራጭ ሊወሰድ ይችላል።

🔴 ከፍተኛ መረጃ ላይ የተመሰረቱ ጥናቶች ምን ይመክራሉ።

👉 41 ሳምንት ላይ ለእናቶች የምጥ መርፌ መስጠት እና እንዲወልዱ ማድረግ የፅንስ ሞትን እና ከወሊድ በኃላ የሚከሰትን ጊዜያዊ የልጅ የህመም ደረጃ እና ዘላቂ ጉዳትን ይቀንሳል።

👉 ከ41 ሳምንት በላይ ምጥ በራሱ ቢጀምርም በኦፕሬሽን የመውለድ እድል የምጥ መርፌ ከሚሰጣቸው በተጨባጭ ያነሰ አይደለም።

🔴 ለእናቶች መልእክት፦

👉 ከሚጠብቁት የመውለጃ ቀን በላይ የተወሰኑ ቀናት ቢዘገይ ጤናማ እንደሆነ ማወቅ ይኖርብዎታል ፤ ነገር ግን ከ40 ሳምንት በኃላ የክትትል ጊዜ ማሳለፍ የለብዎትም። እርግዝናዎ ከ41 ሳምንት በላይ ካለፈ ከሐኪምዎ ጋር ስለምጥ መርፌ አማራጭ ይነጋገሩ።

ዶ/ር ትዕዛዙ ዓለሙ: የማህፀን እና ፅንስ ስፔሻሊስት

Telegram: t.me/HakimEthio

‎X jedhamti umurii ishee waggaa 25 fi dhalattee kan guddattee maatii muslimaa fi  tikfattootaa keessatti. X heerumtee ji...
11/08/2026

‎X jedhamti umurii ishee waggaa 25 fi dhalattee kan guddattee maatii muslimaa fi tikfattootaa keessatti. X heerumtee jirti amma haadha ijoollee 3ti, Abbaa warraa fi ijoollee ishee wajjinis jiraachaa jirti.

‎X yeroo baayyee kophaa ishee ijoollee umuriin waggaa 10 hin guunne wajjin mana keessaa hojii manaa dalagaa oolti. Abbaan warraa ishee hojii re'ootaa fi Gaala tiksuuf lafa karaa dheeraa oolee gala. Osuma kanaan jiranuu, amalli (behavior) X tasuma jijjiirrame.

Hirriiba dhabuu eegalte, ni lolti, waan xiqqoof dheekkamti, ni aarti, ijollee reebuu eegalte, uffata ofirraa baastee darbuu yaaddi, sagalee dheeradhan iyyiti, akka nama waa yaamuu gooti, Manaa baatee baduuf yaalti, yaalii of-ajjeesuu (Su***de attempt) illee taasiste turte.

Maatin X fi firoinni bitaa itti galeera. Hanga ammatti maatin X gara mana yaalaa osoo ishee hin geessine akkanumaan baatin tokko kuteera, Garuu yaala aadaa (traditional treatment method) adda addaa hoomtuu isaan hin hafne.

‎Amma luul dhukkubni ishee gara biraatti jijjirramee jira.

‎Hirriiba durumaanu akkuma dhabdetti jirti. Nyaata nyaachuu didde. Kan dur afaanin (verbally) dheekkamtu sun amma guutumatti dubbii dhaabde (mute) ija dhumaan nama ilaalti, kanumaan osoo jirtuu sochii godhuullee dadhabde, yoo teesse ol ka'uu hin feetu, yoo dhaabatte gad taa'uu hin feetu, konkolaataa keessattillee dhaabattee konkolaatan deeman.

Ammaa X erga fayyaa dhabdee baatii 2 bira kuteera, guyyaa tokko maatin X, X gara hospitaala geessuf murteessan. Hospitaaluchis yaalii godheefi gara mana isheetti deebise. X garuu fayyuu hin dandeenye.

X guyyaa tokko hospitaala ani keessti dalagu Gashamo Hospital jedhamutti fidanii naaf dhufan. Yeroo kana X ulfaatina baayyee hirristee jirti(whieght loss) gootee jirti, wheelchair dhaan sochoosaa Emergency opd fidan, hin dubattu, hin nyaattu, hin raftu, hin sochootu.

‎Yeroma sana team koo wajjin taanee support care gargaarsa duraa barbaachisaa ta'an hunda goonef, itti fufnees,History ykn akkaataa dhukkubashii akka armaan olitti erga aranne, booda investigashinii barbaachisaa ta'an gara laboratooriitti goonefii booda bua'aan qorannoo laaboratoorii norman average ta'ee dhufe.

Amma erga Diagnosis goonee booda qorichoota dhukkuba kanaaf kennaman karaa hidda dhiigaa (IV) challenge dhaan eegalle, hirriibaa gaarii rafuu eegalte, guyyaa tokko keessatti jijjiiramni mul'ataa dhufe.

Guyyaa lamaaf itti fufnee amma nyaata ofiin soorachuu eegalte, gaafa guyyaa 3ffaa limmee kana irraa dhiisnee kiniina jijjiirref, amma socha'uullee eegalte, afaanin dubachuus yaalte, waan namni jedheen fudhachuu eegalte, ol jettee mana fincaanii deemuu eegalte,.

Gaafa guyyaa 4ffaa maaliif akka hospitaala ishee fidan gaafachuu eegalte, maal ta'een na fiddan jechuun dhufe, ijoollee ishee illee eessa akka jiran gaafachuu eegalte. Gaafa guyyaa 5ffaa guuttu mooraa hospitaalaa keessa kophaa sochawuu eegalte, ijoollee koo yaade jechuun dhufe, yaalumsi keenya ni milkaaye.

History dhukkuba X gara jalqabaa keessatti Dhukkuba gosa psychosis tu sababa dhukkuba gara dhumaa kanaa ta'uu waan argineef isa kana yaalun dirqama waan ta'eef, Kiniina bareedaa isaa wajjin gara mana isheetti discharge goonerra. Maatin X gamadanii nu eebbisanii galan.

‎Ergaa gabaabduu tokkon qabna. Yaa Uumata keenya yoo xiqqaate dhukkuba sammuu arifachiisa (ድንገተኛ) akkana osoi iddoo adda adda dhiistanii osoo gara hamaatti (severe) hin jijjiirramiin atattamaan gara mana yaalaa geessu qabdu.

Dhukkubni xiqqoo hin qabdu, akkuma dhukkuba Sukkaaraa (DM) fi Dhiibbaa dhiigaa (HTN) yaalamani fayyan, dhukkubni sammuus yaala qaba. Ni fayyas Fayyaan sammuu fayyaa hundaa caala. ‎Ogeessa fayyaa sammuu

Ofisa Zewde
‎Hospitaala Gashamo irraa.

Telegram: t.me/HakimEthio

ድንገተኛ የህፃናት ተደጋጋሚ የሆድ ቁርጠት መንስኤ❗️ ✔️ የአንጀት ውስጥ እርስ በእርስ መደራረብ አብዛኛውን ጊዜ  ህፃናት ላይ የሚስተዋል የጤና እክል ሲሆን የሚከሰተውም  የላይኛው የአንጀት...
11/08/2026

ድንገተኛ የህፃናት ተደጋጋሚ የሆድ ቁርጠት መንስኤ❗️

✔️ የአንጀት ውስጥ እርስ በእርስ መደራረብ አብዛኛውን ጊዜ ህፃናት ላይ የሚስተዋል የጤና እክል ሲሆን የሚከሰተውም የላይኛው የአንጀት ክፍል ልክ እንደ ቴሌስኮፕ የታችኛው የአንጀት ክፍል ውስጥ በተለያየ ምክንያት እንዲሁም ያለምንም ምክንያት እርስበርስ ተደራርቦ እና ተቀርቅሮ ሲቀር ነው። ይህም ችግር በህክመናው Intussusception በመባል ይታወቃል።

✔️ ታድያ ይህ ክስተት በጊዜ ካልታከመ የአንጀት የደም ዝውውርን በማቋረጥ የአንጀት መሞትን እንዲሁም ከባሰ የአንጀት መበስበስ እና መበሳት ከዛም በጤናማው መንገድ መወገድ ያለበት የአንጀት ውስጥ ቆሻሻ የሆድ እቃ ውስጥ በመፍሰስ እና የሆድ እቃ ግድግዳ ብግነትን በማስከተል የልጆችን ሂወት በአጭር ጊዜ ውስጥ አደጋ ላይ ይጥላል።

✔️ ይሄ የጤና እክል በብዛት እድሜያቸው ከ 6 ወር እስከ 3 አመት ያሉ ህፃናት ላይ በተለይ ከቫይረስ ጋር በተያያዘ የጉንፋን ወይም የተቅማጥ ህመም ከተከሰተተ በኋላ ሲከሰት ይስተዋላል።

✔️ በዋነኝነት የሚታዩት ምልክቶች

👉 ለጥቂት ደቂቃዎች የሚቆይ ሁለት እግራቸውን ወደ ሆዳቸው የሚያሳጥፍ ሀይለኛ የሆድ ቁርጠት መኖር እንዲሁም ከህመሙ በኋላ በመሀል ደግሞ ደህና መሆን እና ያለ ምንም የህመም ምልክት ወደ ጨዋታቸው መመለስ እና ከዛም ከትንሽ እረፍት በኋላ ተመሳሳይ የሆነ የሆድ ህመም እየደጋገመ መከሰት

👉 ከህመሙ ጋር ተያይዞ የበሉትን ማስመለስ እና ላብ ማላብ እንዲሁም ከመጠን በላይ ማልቀስና መወራጨት

👉 የሰገራ ደም መቀላቀል ወይም የተዝለገለገ ደም የቀላቀለ ፈሳሽ እንዲሁም አንዳንዴ ከባሰ አንጀት በፊንጢጣ በኩል መውጣት

👉 የሰገራ መውጣትን መከልከል

👉 የሆድ መንፋት ወይም እብጠት መኖር ናቸው ።

✔️ ታዲያ ወላጆች እነዚህን የጠቀስኳቸውን ምልክቶች ካስተዋላቹ የልጅዎ ሂወት አደጋ ላይ ከመውደቁ በፊት በጊዜ ወደ ጤና ተቋም ልጅዎን መውሰድ ያስፈልጋል።

✔️ በጤና ተቋም የመላው እና የሆድ አካላዊ ምርመራ፣ የደም ምርመራ እና የሆድ አልትራሳውንድ ምርመራ በማድረግ ችግሩ መኖር አለመኖሩ መታየት ያስፈልገዋል።

👉 የሚሰጠው ህክምና እንደተገኘው ውጤት እና ልጁ እንዳለበት የጤና ሁኔታ ይለያያል። ማለትም

1️⃣ ያለምንም ህክምና በቀጠሮ በክትትል በማድረግ

2️⃣ ያለቀዶ ህክምና በፊንጢጣ በኩል በለስላሳ ቀጭን ቱቦ በሚሰጥ ፈሳሽ ወይም አየር የተደራረበውን የአንጀት ክፍል ወደ ጤናማው ቦታው እንዲመለስ በማድረግ እንዲሁም ደግሞ

3️⃣ እንደ አስፈላጊነቱ በቀዶ ህክምና እንዲታከም ይደረጋል።

👉 በዋነኝነት የቀዶ ህክምና የሚያስፈልግባቸው ሁኔታዎች

✔️ ህፃኑ በጊዜ ወደጤና ተቋም ሳይሄድ ወይም በተገቢው ምርመራ ችግሩ ሳይታወቅለት ቀርቶ ችግሩ የተከሰተበት የአንጀት ክፍል የተጎዳ ከሆነ እና የሆድ እቃ ግድግዳ ብግነት ከተከሰተ

✔️ በአልትራሳውንድ ምርመራ ሲታይ መንስኤ የሆነው ችግር ከታየ

✔️ በፈሳሹ ወይም በአየሩ ህክምና የአንጀት መደራረቡ ወደ ጤናማ ቦታው የመመለስ ተስፋ ከሌለው ወይም ተያይዞ የአንጀት መበሳት ከተከሰተ ነው።

👉 ታዲያ በቀዶ ህክምና ጊዜ የተደራሪበው አንጀት ክፍል ሲላቀቅ የአንጀቱ ክፍል የበሰበሰ ወይም የተበሳ ከሆነ የተበላሸውን ክፍል ቆርጦ ማውጣት እና የቀረውን የአንጀት ክፍል በመቀጣጠል መስፋት ያስፈልጋል።

👉 ነገርግን የተበላሸው የአንጀት ክፍል ከወጣ በኋላ የቀረው የአንጀት ክፍል የበገነ ወይም ያበጠ ከሆነ እንዲሁም ህፃኑ ላይ ተፈጠረበት ኢንፌክሽን ደረጃው ከፍ ያለ ከሆነ አንጀቱን እርስ በእርስ ለመስፋት ወይም አንጀቱን ለመቀጣጠል ስለማይቻል ለጊዜው ሰገራ ማውጫ በጎን ሆድ እቃ ግድግዳ በኩል ማውጣት ያስፈልጋል ።

👉 ከዛም አንጀቱ ወደ ጤንነቱ ሲመለስ እና የልጁ ጤንነት እንዲሁም ሰውነቱ ከህመሙ እና ከቀዶ ህክምናው ሲያገግም ከተወሰነ ጊዜ በኋላ አንጀቱን ወደ ቦታው መልሶ እንዲሰፋ እና ወደ ጤናማ ስራው እንዲመለስ ይደረጋል።

✅ ስለዚህ በአጠቃላይ ለወላጆች የምመክረው ልጃቹ ላይ ተደጋጋሚ የሆነ የሆድ ቁርጠት መኖር እና ከህመሙ ጋር ተያይዞ የበሉትን ማስመለስ ካለ እንዲሁም ደም የቀላቀለ ካካ ካስተዋላቹ በአፋጣኝ ወደ ጤና ተቋም በመሄድ የሆድ አልትራሳውን ምርመራ ልጅዎን ማስመርመር እና ችግሩ በዋነኝነት የአንጀት እርስበርስ መደራረብ መሆን አለመሆኑን ማረጋገጥ ያስፈልጋቹሀል ማለት ነው።

ማጣቀሻ - Coran Pediatric Surgery 7th Edition

ዶ/ር ዮናታን ከተማ: በቅዱስ ጳውሎስ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የህፃናት ቀዶ ህክምና ሬዚደንት ሀኪም

ሰላምና ጤና በያላችሁበት ይሁን!

ለበለጠ ማብራሪያ 👇👇👇 መጎብኘት ይችላሉ።
YouTube - https://youtube.com/?si=4k6s0RROG_lVCA3u

የስኳር በሽታና እና የአይን ጤናየስኳር በሽታ ትናንሽ የደም ስሮችን ከሚያጠቃባቸው ዋንኛ የሰውነት አካሎቻችን አንዱና ዋንኛው አይናችን ነው። በዚህ ፅሁፍ የስኳር በሽታ እንዴት የአይን ጤናን ...
11/08/2026

የስኳር በሽታና እና የአይን ጤና

የስኳር በሽታ ትናንሽ የደም ስሮችን ከሚያጠቃባቸው ዋንኛ የሰውነት አካሎቻችን አንዱና ዋንኛው አይናችን ነው። በዚህ ፅሁፍ የስኳር በሽታ እንዴት የአይን ጤናን እንደሚያናጋ (በዋናነት የስኳር ሬቲና በሽታን (Diabetic retinopathy))፣ እነማና የበለጠ ተጋላጭ ናቸው፣ ስንት አይነት የስኳር ሬቲና በሽታ አለ፣ምልክቶቹ እና መፍትሄውስ እሚለውን እንመለከታለን።

የስኳር በሽታ እንዴት የአይን ጤናን ያናጋል?

የደም የስኳር መጠን ከተለመደውና መሆን ካለበት መጠን በላይ ሆኖ ለረጅም ጊዜያት በሚቆይበት ጊዜ ለእይታ የሚያገለግለን የውስጠኛው የአይናችን ክፍል ላይ የሚገኙ ጥቃቅን የደም ሰሮች ህዋሳትን በመጉዳት፣ በመግደል፣ ህብርነታቸውን በማሳጣት በዉስጣቸው የሚያለፍው ደም ከደም ቧንቧ ሾልኮ በመውጣት ሬቲና እሚባለው የአይናችን ክፍል ላይ እንዲረጭ ያደርጋል። ከዚህም ባስ ሲል የውስጠኛውን የአይን የደም ስር በማጥበብ እሚፈሰውን የደም መጠንና የኦክስጅን አቅርቦት በማሳነስ አዳዲስ ደካማ፣ ደም ወደ ውጪ እንዲፈስና ሬቲና እንዲያብጥ የሚያደርጉ የደም ስሮች እንዲፈጠሩ ምክንያት ይሆናል።

ከላይ ከተጠቀሱት በተጨማሪነት የስኳር በሽታ የሌንስን ጥራት በማሳጣት የአይን ሞራ እንዲከሰት ያደርጋል።

እነማና የበለጠ ለስኳር የሬቲና በሽታ (Diabetic retinopathy) ተጋላጭ ናቸው?

* ደካማ የሆን የስኳር መጠን ቁጥጥር ያላቸው ታካሚዎች
* ለረጅም አመታት ከስኳር በሽታ ጋር የቆዩ ታካሚዎች
* በተጨማሪነት የደም ግፊት በሽታ ያላቸው (75% ያህል በሚሆኑት ይህ በሽታ ይከሰትባቸዋል)
* ከፍተኛ የሆነ የኮሌስትሮል መጠን ያላቸው እንዲሁም (50% ያህል በሚሆኑት ይህ በሽታ ይከሰትባቸዋል)
* ሲጃራ ማጤስ የበለጠ ተጋላጭነትን ይጨምራል።

ስንት አይነት የስኳር ሬቲና በሽታ አለ?

በዋንኛነት ሁለት አይነት የስኳር ሬቲና በሽታዎች አሉ
1. የደም ስር ያላበቀለ (Non prolifrative diabetic retinopahty)፦ በዚህኛው ስር የሬቲና ደም ስሮች ህዋሳት ተጎድተው፣ ህብርነታቸውን አጥተው፣ አንዳንድ ቦተዎች ላይ ወደ ውጪ አብጠው (Microaneurysms) ባስ ሲልም ደም እረጭተው የሚገኝበት ነው። ነገር ግን በዚህኛው አይነት ስር ምንም አይነት አዳዲስ የደም ስሮች በቅለው አናገኝም።

2. የደም ስር ያበቀለ (prolifrative diabetic retinopahty)፦ በዚህኛው ስር በዋናነት አዳዲስ የደም ስሮች በቅለው የሚገኝበት ነው።

ምልክቶቹ ምንድን ናቸው?

90% እሚሆኑ የዚህ በሽታ ተጠቂዎች የበሽታው ምልክት እማያጋጥማቸው ሲሆን ሲከሰት ግን
* የእይታ ብዠ ማለት
* ቀለማትን ለመለየት መቸገር
* የእይታ መቀነስና ማጣት
* የአይን ግፊትን በመጨመርና ግላኮማን በማምጣት የአይን ውስጥ ህመም መፈጠር
* አይናችን ውስጥ እንደፀጉር ያለ ውር ውር እሚሉ ነገሮችን መመልከትን ያጠቃልላል

መፍትሄውስ?

መከላከሉንና መፍትሄውን ስንመለከት አራት አይነት ስትራቴጂዎች ይኖሩናል

ሀ. አጠቃላይ ህክምና
*ታካሚዎች የደም ስኳርን፣ HbA1cን፣ የደም ግፊታቸውንና የኮሌስትሮል መጠናቸውን በየጊዜው መለካትና ማወቅ
*የልብ፣ የኩላሊትና የነርቭ መርመራዎችን ማድረግ ሲኖርባቸው ከነዚህ በተጨማሪነት

1. የስኳር መጠናቸውን መቆጣጠር። እንዴት?
* ከሀኪም ጋር በመነጋገር አመጋገብን ማስተካከል
* መድሀኒትን በተገቢው ሰዓትና ተገቢውን መጠን መውስድ
* ቋሚና ተከታታይነት ያለው የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ማድረግ

2. የደም ግፊት ፣ የኮሌስትሮል መጠኖን መቆጣጠር

3. ሲጃራ ማጤስ ማቆም

4. የክትትል ጊዜዎን ሳያዛንፉ ሀኪሞን መጎብኘትና የደም ስኳር መጠኖን መለካት።

ለ. የመድሀኒት ህክምና ለስኳር ሬቲና በሽታ

- በሽታውን ተከትሎ የሚመጡ አዳዲስ የሬቲና የደም ስር እድገቶችን እሚከላከል፣ያሉትንም የሚያጠፋልን፣ የማዕከላዊ ሬቲና እብጠትን(Diabetic macular edema) የሚያሟሽሽልን በአይን ውስጥ በመርፌ እሚሰጡ የተለያዩ መድሀኒቶችን በአይን ሀኪም እንዲሰጥ በማድርግ እይታን መጠበቅ።

ሐ. የጨርር ህክምና
ጨረርን በመጠቀም አላስፈላጊ አዳዲስ የበቀሉ የደም ስሮችን እንዲከስሙ ያደርጋል።

መ. ቀዶ ህክምና
በቀዶ ህክምና፤ በሽታውን ተከትሎ የፈሰሰ ደም ካለና በራሱ መጥራት ሲገባው ሳይጠራ ለረጅም ጊዜ ሲቆይ ማጠብ፣ ከሬቲና ተያይዘው ያሉና እየሳቡ ያሉ ነገሮችን ማላቀቅና ሬቲናው ከቦታው ተላቆ ካለ መመለስ።

** ቀዶ ጥገና አንዱ የህክምና አማራጭ ቢሆንም ነገር ገና እይታ ጥርት ብሎ እንደድሮ አለመመለስ፣ ቁስሉ በቶሎ አለመዳን እንዲሁም ቁስለት የመያዝ ነገሮች ሊያጋጥሙ ይችላሉ።

*** በስኳር በሽታው የተነሳ ሞራ ሰርቶ ካለ በቀዶ ጥገና መገፈፍ ይኖርበታል።

መቼ የአይን ሀኪም ይጎብኙ?

የስኳር በሽታ ታካሚ ከሆኑ ምንም አይነት የእይታ መረበሽ ባይኖርቦትም እንኳ የአይን ሀኪም ጋር ሄደው መታየት አለቦት። መቼ?

* አይነት ሁለት የስኳር በሽታ እንዳለቦ ካወቁ የመጀመሪያ የአይን ምርመራዎን ወዲያውኑ የአይን ሀኪም ጋር በመሄድ ማድረግ አለቦት።

* አይነት አንድ ያለቦት ከሆኑ እንዳለቦት ባወቁ በ5 አመታት ውስጥ የመጀመሪያ የአይን ምርመራዎን ማድረግ አለቦት።

***በማንኛውም የጤና ተቋማት ውስጥ ያሉ ባለሙያዎች የስኳር በሽታ ታካሚዎቻቸው የአይን ምርመራን በተገቢው የጊዜ ሰሌዳ ማድረጋቸውን ማረጋገጥ፣ ያላደረጉትን እንዲያደርጉ ማበረታታትና ወደአይን ሀኪም ጋር በመላክ የስኳር ሬቲና በሽታን መከላከልና ተገቢውን ህክምና እንዲያገኙ ማድረግ ይቻላል።

ዶ/ር በእምነት ተረዳ ፤ የአይን ህክምና ስፔሻሊስት

Telegram: t.me/HakimEthio

These days, AI, social media, and different kinds of technology have become part of our everyday lives. There’s no doubt...
10/08/2026

These days, AI, social media, and different kinds of technology have become part of our everyday lives. There’s no doubt that they have improved the way we live, made many things easier, and helped us solve problems in almost every aspect of life.

The same is true for healthcare and medicine, where technology and AI are opening up even more promising possibilities for the future.
But alongside these benefits, there are also some worrying consequences.

One thing I’ve personally noticed is the amount of misinformation and unproven, sometimes dangerous, traditional medical practices being shared across social media platforms, especially on TikTok, Telegram, and Facebook. I’ve also come across AI-generated fake videos using the faces or voices of well-known doctors and celebrities to promote certain products or make misleading health claims.

This can be quite dangerous. Many people may not have the medical knowledge or time to verify whether what they see online is actually true. And once this kind of content goes viral, correcting it can be much harder.

As we know, the algorithms of most social media platforms are largely driven by engagement—likes, shares, comments, and views. Unfortunately, the algorithm doesn’t necessarily care whether the information is accurate or harmful as long as people are engaging with it.

Some platforms do have systems to identify misinformation and misleading content, but from what I’ve seen, these systems still seem to struggle with a lot of health-related content coming from our country. Language barriers and other local factors may also play a role.

Whenever I come across concerning health-related content, I try to respond or leave a comment when possible. I’ve also seen several people consistently doing the same, and I really appreciate their efforts. But perhaps we need something more organized.

I think it would be valuable to have a dedicated medical fact-checking platform or body that can quickly review and verify viral health claims and provide evidence-based information to the public. Something similar in spirit to the work journalists like Elias Meseret have been doing in fact-checking and addressing misinformation in other areas.

This is just an idea, and I’m sure there are better approaches that I may not have considered.

I’d really like to hear your thoughts, suggestions, and alternative ideas.

How do you think we can better address the spread of health misinformation across social media platforms, particularly with the emerging challenge of AI-generated medical misinformation in Ethiopia?

Nathnael Toga (MD)

Telegram: t.me/HakimEthio

Successful Surgical Removal of a Giant Anterior Mediastinal ThymolipomaA 26-year-old man presented to EthioTebib Hospita...
10/08/2026

Successful Surgical Removal of a Giant Anterior Mediastinal Thymolipoma

A 26-year-old man presented to EthioTebib Hospital with a one-year history of progressive shortness of breath on exertion, intermittent dry cough, easy fatigability, and nonspecific chest discomfort, with worsening symptoms over the preceding four months. He also reported episodes of breathlessness while lying flat. He had no history of smoking, pulmonary tuberculosis, chronic medical illness, or occupational exposure.

Comprehensive evaluation, including chest CT imaging and CT-guided core needle biopsy, revealed a giant anterior mediastinal fatty mass causing significant compression of the surrounding mediastinal structures. Following multidisciplinary assessment, the patient was scheduled for definitive surgical excision.

Our Cardiothoracic Surgery team successfully performed a median sternotomy with complete excision of the mediastinal mass.

Intraoperatively, the tumor was found to extend into both sides of the mediastinum, with the bulk occupying the left hemithorax. Careful dissection and ligation of the feeding vessels enabled complete removal of the mass while preserving the surrounding vital structures. A mediastinal drain was placed, and the procedure was completed successfully without intraoperative complications.

Intraoperative images uploaded on t.me/HakimEthio

The patient had an uneventful postoperative recovery with marked improvement in his respiratory symptoms.

Follow-up chest radiography demonstrated expected postoperative findings, including minimal bilateral pleural effusion with the chest tube in situ.

Histopathological examination of the excised specimen confirmed thymolipoma with no evidence of malignancy.

This case highlights Ethio Tebib Hospital's expertise in the diagnosis and management of complex thoracic conditions through advanced imaging, multidisciplinary collaboration, and specialized cardiothoracic surgery. Equipped with experienced specialists and modern surgical facilities, we continue to provide safe, comprehensive, and patient-centered care for patients with even the most challenging thoracic diseases.

Acknowledgment

We extend our appreciation to Dr. Abebe Bezabih (Cardiothoracic Surgeon), Dr. Khalid Arebo (General Surgeon), and the entire surgical team for their expertise, seamless collaboration, and dedication in delivering outstanding patient care.

📞For more information and to schedule an appointment, call +251933745555 or call our toll-free number 9000.

📍Our address is located on the road leading to Kolfe, Masalemiya Sefereselam.

📱Telegram 📱Tiktok 📱Facebook 📱Instagram 📱Youtube

𝐄𝐭𝐡𝐢𝐨-𝐓𝐄𝐁𝐈𝐁 𝐇𝐨𝐬𝐩𝐢𝐭𝐚𝐥
We strive for your health!!

‎My Dear C-1 Students,🩺🩺‎‎Receiving this certificate from you is one of the most meaningful honors of my academic career...
10/08/2026

‎My Dear C-1 Students,🩺🩺

‎Receiving this certificate from you is one of the most meaningful honors of my academic career. It is not merely a piece of paper—it is a reflection of the trust, respect, and shared journey we have had in the classroom. For that, I sincerely thank each one of you.

‎🩺Teaching is not only about transferring knowledge; it is about inspiring minds, nurturing character, and preparing future professionals who will serve humanity with competence and compassion. Seeing your appreciation reassures me that our efforts together have been worthwhile.

‎🩺As you now embark on your clinical years, always remember that medicine is a profession of lifelong learning, humility, discipline, and service. Never stop asking questions. Never compromise your integrity. Treat every patient with dignity, empathy, and respect, because every patient is someone's beloved family member.

‎🩺Let your knowledge be guided by evidence, your decisions by ethics, and your actions by compassion. Excellence is not achieved in a single examination or clerkship—it is built through consistent dedication every single day.

‎🩺I have every confidence that each of you has the potential to become not only an outstanding physician but also a leader, educator, researcher, and advocate for better healthcare. Continue striving for excellence, support one another, and never lose the passion that brought you into medicine.

‎🩺Thank you once again for this unforgettable recognition. Your appreciation will remain in my heart, and I will always be proud to have been part of your journey.

‎🩺I wish you every success in your clinical training and beyond. May your white coats always symbolize knowledge, humility, integrity, and compassionate service to humanity.

‎With immense pride and gratitude,

‎Mesud Mohammed
‎Clinical Pharmacy Specialist | Lecturer |Researcher | Certified Medicine Information Expert | Pharmacy Academic & Clinical Service Director, MWU-CMHS-GRH

‎Take this one 🤜🤛
‎"The art of medicine is to cure sometimes, treat often, and comfort always." (Hippocrates)

Telegram: t.me/HakimEthio

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Hakim posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share