Ethiopian health today

Ethiopian health today Ethiopian Health Today is for awareness creation: health, education,foreign relation,Aid organizations,and professional development.

University of Gondar GP contract appointment 80 GP needed
08/05/2026

University of Gondar

GP contract appointment

80 GP needed

ቅዱስ ጴጥሮስ ሆስፒታል / Kidus Petros Hospital ዝውውር
08/05/2026

ቅዱስ ጴጥሮስ ሆስፒታል / Kidus Petros Hospital

ዝውውር

WSU College of Health Science and Medicine - ወሶዩ ጤና ሳይንስና ሕክምና ኮሌጅ
08/05/2026

WSU College of Health Science and Medicine - ወሶዩ ጤና ሳይንስና ሕክምና ኮሌጅ

08/05/2026
 university
08/05/2026

university

University of Gondar
08/05/2026

University of Gondar

08/05/2026

አሁን የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ G*T ተፈተኑ ማለቱ ምንድን ነው?
የጤናውን ስርዓትኮ እንዴት ውስብስብ እንዳደረግነው ይገርማል🤔....Exit Exam....COC....Matching Exam.... National G*T Exam..... AAU G*T Exam......ከዛስ??
እንበልና የሆነ ሰው National G*T exam አልፎ AAU G*T exam ባያልፍ ምን ሊያደርጉት ነው??🤔

👇 መግለጫ
08/05/2026

👇 መግለጫ

የመጀመሪያዋ ሴት የህክምና ፕሮፌሰርፕሮፌሰር የወይንሐረግ ፈለቀ ይባላሉ፡፡የመጀመሪያዋ ሴት የህክምና ፕሮፌሰር ናቸው፡፡ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ታሪክ ደግሞ ይህንን ማዕረግ በማግኘት የቀደሟቸ...
08/05/2026

የመጀመሪያዋ ሴት የህክምና ፕሮፌሰር

ፕሮፌሰር የወይንሐረግ ፈለቀ ይባላሉ፡፡የመጀመሪያዋ ሴት የህክምና ፕሮፌሰር ናቸው፡፡ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ታሪክ ደግሞ ይህንን ማዕረግ በማግኘት የቀደሟቸው አንድ ሴት ብቻ ናቸው፡፡ በመምህርነት፣ በተማራማሪነት እና በሀኪምነት ላለፉት 33 ዓመታት እያገለገሉ ይገኛሉ፡፡ የስኳር ህመምን የተመለከተ አንድ መጽሐፍም አሳትመዋል፡፡

በ1977 ዓ.ም የዶክትሬት ዲግሪያቸውን ያገኙት ፕሮፌሰር የወይንሐረግ ለአምስት ዓመት በጠቅላላ ሀኪምነት አገልግለዋል፡፡ ለአራት ዓመት የዘለቀውን የድህረ ምረቃ ትምህርታቸውን ደግሞ በውስጥ ደዌ ህክምና ተከታትለዋል፡፡ ከተመረቁ በኋላ በዚያ በተማሩበት ዩኒቨርስቲ በአስተማሪነት እንዲቀሩ ሲመረጡም በትምህርት ክፍሉ ብቸኛዋ ሴት ነበሩ፡፡ ፕሮፌሰር የወይንሐረግ የምርምር ስራዎችን የጀመሩትም ከዚያን በኋላ ነው፡፡
“ሜዲካል ዶክተር ሆኖ እንደገና ተመልሶ የውስጥ ደዌ ስፔሻሊስት ስሆን አንድ የመጀመሪያ ብቸኛ ሴት ነው የነበርኩት፡፡ ወደ 23 ወንዶች ነበር የነበሩት፡፡ ትምህርት ክፍሉ ውስጥተወዳድሬ ነው የቀረሁት፡፡ ተመልሼ የገባሁት በቀለም ሲኮተኩቱኝ የቆዩ አስተማሪዎቼ ጋር ነው፡፡ እንግዲህ ከባድ እና ፈታኝ ነው ግን በዚህ ልክ እንደገባሁ የእኔ የበላይ አለቃ የነበሩት አሁን በህይወት የሌሉት ፕሮፌሰር ጀማል አብዱልቃድር ወደ ምርምሩ ዘርፍም እንደገባ አደረጉኝ፡፡ ቶሎ ነው፣ በገባሁ በሶስተኛ ቀን ነው ወደ ምርምር ዘርፍ ሀሳቤ እንዲያደላ ያደረግሁት፡፡ ስለዚህ እኔ በቃ አንዳንድ ተግዳሮቶች ቢኖሩም ግን አማራጭ መንገዶችን በማየት ማለፍ ይኖራል” ይላሉ ምሁሯ፡፡

እንዲህ የተጀመረው የፕሮፌሰር የወይንሐረግ የምርምር ስራ በርካታ ውጤቶቸ የተመዘገቡበት ሆኗል፡፡ ወደ 65 ገደማ የምርምር ጽሁፎችን ማዘጋጀታቸውን የሚናገሩት መምህሯ 52 የሚሆኑቱ በተለያዩ የምርምር መጽሔቶች (ጆርናሎች) ላይ መታተማቸውን ያስረዳሉ፡፡ አብዛኞቹ የጥናት ስራዎቻቸው በስኳር በሽታ እና ተያያዥ የሆርሞን ህመሞች ላይ ያተኮሩ ናቸው፡፡ የዚህ ምክንያቱ ደግሞ ስፔሻላይዝድ ያደረጉበት ሙያቸው እንደሆነ ይናገራሉ፡፡ የውስጥ ደዌ ስፔሻሊስት የሆኑት ፕሮፌሰር የወይንሐረግ በስኳር ህመም እና ሆርሞን ህመሞች ላይ ህክምና እየሰጡ ይገኛሉ፡፡

ፕሮፌሰር የወይንሐረግ በህብረተሰቡ ዘንድ ስለስኳር ህመም ያለው ግንዛቤ ያደግ ዘንድ ሰለበሽታው የሚያወሳ መጽሐፍ በአማርኛ ቋንቋ አሳትመዋል፡፡ ከ10 ዓመት በፊት ለንባብ የበቃው ይህ መጽሐፍ በ11 ሺህ ቅጂ ተባዝቶ ተሰራጭቷል፡፡ ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢም ለጥቁር አንበሳ ሆስፒታል እንዲውል መለገሳቸውን ይናገራሉ፡፡ መጽሐፉን በሚያዘጋጁበት ጊዜ ጎን ለጎን የስኳር ህመም እና የህሙማን እንክብካቤ ምን እንደሚመስል የሚገመግም ጥናት አካሄደዋል፡፡ ይህ በአዲስ አበባ በሚገኙ አምስት ሆስፒታሎች እና 21 ጤና ጣቢያዎች ላይ የተካሄደው ጥናትም ሀገር ውስጥ በሚታተም ጆርናል ላይ ለንባብ በቅቷል፡፡
አንጋፋዋ ምሁር ከምርምር ጋር ያላቸው ቁርኝት በዚህ ብቻ የተገደበ አይደለም፡፡ የሚያስተምሯቸው ወጣቶች ተመራማሪዎች እንዲሆኑ ያግዛሉ፡፡ በጥናቶቻቸው ላይ በመሳተፍም የምርምር ውጤቶችን በጋራ ያሳትማሉ፡፡ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የህክምና ትምህርት ክፍል ላለፉት 25 ዓመታት እያስተማሩ የሚገኙት ፕሮፌሰር የወይንሐረግ መምህርነታቸውን እንደሚወዱት ይናገራሉ፡፡

ፕሮፌሰር የወይንሐረግ በማስተማሩ፣ በምርምሩ እና ህክምናው ብቻ ተወስነው አልቀሩም፡፡ ያላቸውን የተጣበበ ጊዜ እንደምንም አብቃቅተውም ቢሆን በተለያዩ የሙያ ማህበራት በቦርድ እና በስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባልነት ይሳተፋሉ፡፡ አባል በሆኑበት የኢትዮጵያ ህክምና ማህበር ፕሬዝዳንት እስከመሆን ደረጃ ደርሰዋል፡፡ ከተመሰረተ 56ኛ ዓመቱን በያዘው በዚህ ማህበር ሊቀመንበርነቱን በመያዝም የመጀመሪያዋ ሴት ሆነዋል፡፡ በኃላፊነት ቦታው ከአንድም ሁለት ጊዜ ተመርጠው አገልግለዋል፡፡ በዚህ ወቅትም ከማስተማር ስራቸው ለተወሰነ ጊዜ ፍቃድ በመውሰድ ጭምር ማህበሩን አንድ እርምጃ ለማራመድ ሞክረዋል፡፡ ይህን ጥረታቸውን ከግምት ያስገባው ማህበሩ ሸልሟቸዋል፡፡

ከዚያ በተረፈ sabbatical leave ወስደው ለማህበሩ ብዙ አገልግሎት አድርገዋል፡፡ ማህበሩን በሚመለከት በተለይ የማማከር አገልግሎት በጤና ጥበቃ ሚኒስቴር በሚኖርበት ጊዜ በተለይ ደግሞ ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎችን (NCD) በተመለከተ እርሳቸው ሙያቸውም ያ ስለሆነ እርሱን በተመለከተ ማህበሩን ወክለው እዚያ ቦታ ላይ ተሳትፈው የጤና ጥበቃ ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች ፖሊሲን በመቅረጽ ብዙ አስተዋጽኦ አበርክተዋል፡፡

ዘርፈ ብዙዋ ምሁር ተሳትፏቸው በርካታ፣ አገልግሎታቸውም በየመስኩ ቢሆንም ለእርሳቸው ትልቁ ነገር የሰው ህይወት ማትረፍ እንደሆነ ይናገራሉ፡፡ “ከህይወት በላይ ምንም ነገር የለምና” ሲሉም ያጠቃልላሉ፡፡
✍️Pharma College

08/05/2026

ዱቲ በዝቷል በሎ የቀነሰው መንግስት ሳይሆን ሐኪሙና የጤና ባለሙያው ነው።
መንግስትማ👉 ጥያቂያቸው ምንድነው ብሎ ጠየቀ? ደሞዝ ዝቅተኛ ነው ተባለ ከዛ ምን ይሻላል ተባለ፤ ቢያንስ ዲቲያቸው በአግባቡ እንክፈል ተብሎ ህግ ወጣ። ለአፈፃፀም ተብሎ ወደየሆስፒታሎች ሲላክ የሆስፒታል ዳይሬክተሮችና ስራ አስኪያጆች የየክልል ጤና ቢሮ ሐላፊዎች እና የከተማ ጤና ቢሮ ሐላፊዎች ወዘተ ኧረ ይሄ ሁሉ ለምንድነው የሚከፈለው ብለው ለመንግስት ጥቆማ ሰጡት።😂
መንግስት ሆዬ ኣ.......ተሸወድሁ እንዴት ብሎ እንደገና ሌላ መመሪያ አመጣ በራሱ በጤና ባለሙያው የተጠናና ቆንጆ ነው የተባለለት። ዱቲ ከሆነች ሰዓት በላይ ገብቶ መገኘት ያስቀጣል😂 በሽተኛ ለማዳንም ቢሆን🤔
Look Look......ጤና ሚኒስቴር: ጤና ቢሮ: ሆስፒታል ያላችሁት እናንተው የጤና ባለሙያዎች ናችሁ። ለእናንተው ጥያቄ እንቅፋቶች ራሳችሁ ናችሁ።
መንግስትን አትውቀሱ??
🗯️🗯️🗯️🗯️🗯️ ከኮተታም አስተሳሰብ እንፋታ 🗯️🗯️🗯️
🗯️🗯️🗯️🗯️🗯️🗯️🗯️🗯️🗯️🗯️🗯️🗯️🗯️🗯️🗯️🤔

Address

Zambiya Street
Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethiopian health today posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Ethiopian health today:

Share