25/05/2026
ማርህይወት የእናቶች የህጻናት እና የውስጥ ደዌ ልዩ የህክምና ማዕከል
እራሱ ባስገነባው ባለ 5 ወለል ህንጻ ላይ እንዲሁም ልምድ ባካበቱ ስፔሻሊስት እና ሰብ ስፔሻሊስት ሃኪሞች ደረጃውን በጠበቀ መልኩ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል፡፡
ማዕከሉ በውስጡ እጅግ ዘመናዊ የቀዶ ህክምና ክፍሎች፣ እናቶች ህጻናት እና አዋቂዎች ተኝተው የሚታከሙበት መደበኛ እና ቪአይፒ ክፍሎች፣ አርተፊሻል መተንፈሻ ማሽን ፣ የጨቅላ ህጻናት ጽኑ ህሙማን ክፍልን ጨምሮ እጅግ ዘመናዊ አልትራሳውንድ ፣X- Ray እና የ ተሟላ የላቦራቶሪ ክፍሎች ፣ የ24 ሰዓት የፋርማሲ አገልግሎት፣ የክትባት አገልግሎት፣ የቤተሰብ ምጣኔ አገልግሎት፣ ቢጫ የሆኑ ህጻናት ህክምና ፣ እና መሰል የ ህክምና አገልግሎቶችን እና የጤና ማማከሮችን ን የያዘ የህክምና ማዕከል ነው፡፡
ማዕከላችን ሙሉ በሙሉ የተፈጥሮ ጸሀይ ኢነርጂን በመጠቀም ከአየር ብክለት የጸዳ 24 ሰዓት የማይቋረጥ የኤሌክትሪክ ሀይል ያለው ሲሆን በተመሳሳይ ደግሞ ራሱ ባስቆፈረው የከርሰ ምድር ውሃ ንጽህናው የተጠበቀ ተቋም ለመፍጠር ችሏል።
ማርህይወት የእናቶች የህጻናት እና የውስጥ ደዌ ልዩ የህክምና ማዕከል