Fozia Nasir

Fozia Nasir Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Fozia Nasir, Health & Wellness Website, Addis Ababa.

28/02/2026
11/02/2026

የየካ ወረዳ 02 አስተዳደር ስራ አስፈጻሚ ጽ/ቤት በ2018 በጀት አመት ባለፉት ስድስት ወራት የተከናወኑ ተግባራቶች የነዋሪዎችን የመልካም አስተዳደር ችግር የቀረፈ ነው፡፡

አቶ እስጢፋኖስ በለጠ፡ የየካ ወረዳ 02 ዋና ስራ አስፈጻሚ ጽ/ቤት ሃላፊ

የካ ወረዳ 02 ኮሙኒኬሽን የካቲት 3/2018 ዓ/ም
በየካ ወረዳ 02 አስተዳደር ዋና ስራ አስፈጻሚ ጽ/ቤት በበጀት አመቱ ባለፉት ስድስት የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ከመለየትና ከመፍታት አንጻር፤ ቅሬታ አፈታት አኳያ፤የአገልግሎት አሰጣጥን ከማሻሻል አኳያ በሌሎችም ዘርፈ ብዙ ስራዎች መሰራታቸውን ገለጸ፡፡

የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ከመለየትና መፍታት፡- በወረዳ ደረጃ ለመፍታት የታቀዱ 2 የተፈቱ 2 አፈፃፀም 100% በበጀት አመቱ ባለፉት ስድስት ወራት በወረዳ አስተዳደር ደረጃ በተፈቱ የመልካም አስተዳደር ችግሮች 10000 ህብረተሰብ ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል፡፡

ደረጃቸውን ጠብቀው የቀረቡ ቅሬታዎች ምላሽ አሰጣጥን ማሳደግ በተመለከተ፡ በመደበኛ ቅሬታ የቀረቡ ቅሬታዎች 2 ውሳኔ ያገኙ 2 አፈፃፀም 100% እንዲሁም በአንድ ማዕከል የቀረቡ አቤቱታዎችና ቅሬታዎች 144 ሲሆኑ የተፈቱ 133 እንዲሁም 11 ለሴክተር ተቋማት ተመርቶ በሂዳት ላይ የሚገኝ መሆኑና አፈፃፀም 92.4%

በ2018 በመጀመሪያ ስድስት ወራት የአንድ ማዕከል አገልግሎት አሰጠጥ ሂዳትን በተመለከተ 98.1% ማድረስ የተቻለ ሲሆን ከባለፈው ከ2017 በጀት አመት አፈጻጸም በ3.2 ፐርሰንት ዕድገት አምጥቷል፡፡

ከተቋማት ቅንጅታዊ አሰራር አንጻር፡-በ2018 በጀት ዓመት በወረዳ ካሉ አምስት የተቋማት ክላስተር ቅንጅታዊ አሰራር እቅድ አቅደው እንዲተሳሰሩ ለማድረግ ታቅዶ 5ቱም ጽ/ቤቶች የተቋማት የትስስር ሰነድ በማዘጋጀት እንዲፈራረሙ ማድረግ ተችሏል ፤የወረዳ ተቋማትን በቅንጅታዊ አሰራር ዙሪያ 2 ጊዜ ምዘና ለማድረግ ታቅዶ 2 ጊዜ ማድረግ ተችሏል አፈፃፀሙ 100% ማድረስ ተችሏል፡፡

ክትትልና ድጋፍ በስልጠና በተደገፋ ሁኔታ 2 ጊዜ ለማድረግ ታቅዶ 2 ጊዜ ማድረግ ተችሏል አፈፃፀሙ 100% ነው፡፡

በ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ስድስት ወራት የግንዘቤ ስርፀት ስራን በተመለከተ በወረዳ ደረጃ በመልካም አስተዳደርና ቅሬታ አቀራረብ አፈታት ስርዓት ዙሪያ ለአመራርና ሰራተኛ እንዲሁም ባለድርሻ አካላት 10 ጊዜ ስልጠና ለመስጠት ታቅዶ በተቀደው መሠረት በወረዳው ውስጥ ለሚኖሩ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ፤ ለተቋማቱ ቅሬታ ሰሚ ኮሚቴዎች፤ ለብሎክ ተወካይ አመራሮች፤ ለመልካም አስተዳደር ፎካል ፐርሰን፤ ለወረዳው የስራ ሃላፊዎች/ቡድን መሪዎችና ሠረተኞች እንዲሁም ለጽ/ቤቱ መማክርት አባላት በተጨማሪም ለወረዳው ምክር ቤት ቋሚ ኮሚቴ አባላት በሙሉ ( በደንብ ቁጥር 143/2015፣ በመልካም አስተዳደር መርሆች፣ በቅሬታና አቤቱታ ሂደት ላይ ፣በመልካም አስተዳደር እቅድ ሪፖርት አዘገጃጀት እና በቅንጅታዊ ስራዎች መመሪያ ላይ ወንድ 408 ሴት 778 ጠቅላላ ድምር 1186 ( አንድ ሺ አንድ መቶ ሰማኒያ ስድስት) ለሚሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎችና ለመንግስት ሠራተኞች ስልጠና የተሰጠ ሲሆን አፈጻጸሙን 100% ማድረስ ተችሏል፡፡

በአጠቃላይ የ2018 በጀት አመት በመጀመሪያ ስድስት ወራት የተጋልገይ እርካታን 92% ማድረስ የተቻለ ሲሆን በተያዘው በጀት አመት የተገልጋይን እርካታ ከፍ ለማድረግ አገልግሎትን በተቀላጠፈ መንገድ በመስጠትና በልዩ ትኩረት በመስራት የበጀት አመቱን የተገልጋይ እርካታ አፈጻጸም 100% በማድረስ የፈረንሳይን የቃል ኪዳን ስምምነት ከግብ ማድረስ ይጠበቅብናል ብለዋል፡፡

15/12/2025

የየካ ወረዳ 02 ሲቪል ምዝገባ የነዋሪዎች አገልግሎት ጽ/ቤት በ2018 በጀት አመት ባለፉት አምስት ወራት ያከናወናቸው ተግባራቶች ከእቅድ አንጻር ሲታይ አመርቂ መሆኑን ገለጸ፡፡

የካ ወረዳ 02 ኮሙኒኬሽን ታህሳስ 05/2018 ዓ/ም

በበጀት አመቱ ባለፉት አምስት ወራት የተሻለ ስራ መሰራቱን የየካ ወረዳ 02 ሲቪል ምዝገባና ነዋሪዎች አገልግሎት ጽ/ቤት ለወረዳው ኮሙኒኬሽን ገልጿል፡፡
ጽ/ቤቱ በበጀት አመቱ ባለፉት አምስት ወራት በበርካታ ዘርፎች የተሻለ አፈጻጸም ማስመዝገቡን የገለጹት የወረዳው ሲቪል ምዝገባና ነዋሪዎች አገልግሎት ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ ብሩክ ግርማ አገልግሎት አሰጣጡን ከቀድሞ በተሻለ መልኩ በማዘመን የወሳኝ ኩነት መርሆዎችን መሰረት በማድረግ የሚከሰቱ ኩነቶችን ትኩረት በመስጠት እና በትጋት በመስራት ነዋሪዎችን በመመዝገብና አገልግሎት አሰጣጡን ቀልጣፋ እና ተደራሽ በማድረግ የነዋሪዎችን እርካታ ከፍ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ኃላፊው አያይዘውም ወቅቱን በጠበቀና የቴክኖሎጂ አሰራርን መሠረት በማድረግና ከሚመለከታቸው አካል ጋር በቅንጅት በመስራት የሲቪል ምዝገባና የነዋሪዎች አገልግሎት ጽ/ቤት ለነዋሪዎች የሚሰጡ አገልግሎቶችን ፈጣንና ቀልጣፋ በማድረግ የነዋሪውን እርካታ ከፍ በማድረግ ከሙስና የፀዳ አገልግሎት ለህብረተሰቡ እያቀረቡ እንደሆነ ጠቅሰው በበጀት አመቱ ባለፉት አምስት ወራት የወሳኝ ኩነት ምዝገባ መረጃና ማስረጃ አሰጣጥ ቅብብሎሽ፤ አቅርቦት እና አጠቃቀምን ከማሳደግ አኳያ 1805 የልደት ምዝገባና ማስረጃ አገልግሎት ለመስጠት ታቅዶ 1978 ተከናውኗል፤166 የጋብቻና ምዝገባ ማስረጃ አገልግሎት ለመስጠት ታቅዶ ክንውን 128 ፤118 የሞት ምዝገባናማስረጃ አገልግሎት ለመስጠት ታቅዶ ክንውን 136 ማድረስ ተችሏል፡፡

የነዋሪዎችን አገልግሎት ማሻሻልና ማሳደግ አንጻር በዘመናዊ ቴክኖሎጅ ነዋሪዎችን መመዝገብ እቅድ 2940 ክንውን 2915፤የነዋሪነት መታወቂያ አገልግሎት መስጠት እቅድ 1891 ክንውን 2819 ፤ እንዲሁም ማኑዋል መታወቂያ አገልግሎት መስጠት እቅድ 0 ክንውን 7 እንዲሁም ለ114 ነዋሪዎች የመሸኛ አገልግሎት ለመስጠት ታቅዶ ክንውን 135 በተጨማሪም ለ16 ነዋሪዎች ዝምድናን ከቅጽ ላይ በማረጋገጥ አገልግሎት ለመስጠት ታቅዶ 31 ማከናዎን ተችሏል፡፡ ለ11 ነዋሪዎች በህይወት ስለመኖር ማስረጃ አገልግሎት ለመስጠት ታቅዶ ክንውን 67 በተጨማሪም ለ1562 የነዋሪዎች የመታወቂያ ስርጭት ለማድረግ ታቅዶ 2203 ተከናውኗል፡፡

እንዲሁም የኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጅን ከማሳደግ አንጻር 750000.00 ወረዳዎች የአገልግሎት የክፍያ ስርዓቱ ዲጂታላይዝ(ቴሌ ብር) ለማድረግ ታቅዶ 763425.00 ማከናዎን ተችሏል ብለዋል፡፡

በመጨረሻም በበጀት አመቱ ባለፉት አምስት ወራት ያለው የእቅድ አፈጻጸም አብዛኛው ከ100% በላይ መሆኑን የገለጹት አቶ ብሩክ ጽ/ቤቱ ባሳለፍነው በጀት አመት የላቀ አፈጻጸም በማምጣት ማጠናቀቁን በማውሳት በ2018 በጀት አመትም በፈረንሳይ የስምምነት ሰነድ በተፈራረምነው የድልን ማስቀጠል ሂደት ከግብ ለማድረስ ደከመኝ ሰለቼኝ ሳይሉ እንደሚሰሩ ተናግረው የነበረውን ድል ማስቀጠል የሚቻለው ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት በመስራት እንደሆነ ገልጸዋል፡፡

Address

Addis Ababa
0000

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Fozia Nasir posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share