08/05/2026
ሚሊኒዬም ጤና አጠባበቅ ጣቢያ የ2018 ዓ.ም የአስር ወር አፈፃፀም ሪፖርት እና ሁለተኛ ዙር የ100 ቀን እቅድ ቀርበው ተገመገመ::
ሚያዚያ 30/2018 ዓ/ም
በመድረኩ ላይ የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ጤና መምሪያ የልማትና ዕቅድ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ አየሌ አረጋዊ፣ የዘርፈ-ብዙ ዳይሬክቶሬት ባለሙያ አቶ ሲሳይ ብሻሩ፣ የጤና ጣቢያው ኃላፊ አቶ ኤፍሬም ተሰማ እንዲሁም የጣቢያው ማኔጅመንት አባላትና ባለሙያዎች ተገኝተዋል።
የውይይት መድረኩን የመሩት አቶ አየሌ አረጋዊ በቀረበው ሪፖርት ዙሪያ ከባለሙያዎች ጋር ሰፊ ውይይት ካደረጉ በኋላ፣ በቀርበዉ ሪፖርት መሰረት ጡሩ አፈፃፀም የታየባቸዉ መለክያዎች(indicators) ተጠናክሮ እንድቀጠሉ እና ዝቅተኛ አፈፃፀም የተመሰገበባቸዉ ተግባራት ላይ የተያዘላቸዉ አቅጣጫ መሰረት በአጭር ግዜ ዉስጥ እንዲተገበሩ አሳስቧል።
የጤና ጣቢያው ኃላፊ አቶ ኤፍሬም ተሰማ በበኩላቸው የሁለተኛ ዙር የ100 ቀናት ዕቅድን ያቀረቡ ሲሆን፣ ዕቅዱ የአስር ወራት የአፈፃፀም መነሻ መዘጋጀቱን ጠቅሶ ዝቅተኛ ውጤት የታየባቸው ተግባራት ላይ ለውጥ ለማምጣት ልዩ ክትትልና ድጋፍ እንደሚያስፈልግም አጽንኦት ሰጥተዋል።
በመጨረሻም የክፍል አስተባባሪዎችና ፎካሎች በተቀመጠው የድርጊት መርሃ-ግብር መሰረት ክፍተቶችን በመሙላት ለተሻለ ውጤት በቁርጠኝነት ለመስራት ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል።
/ጣቢያ
#ሐዋሳ