Hawassa millennium primary health care unit

Hawassa millennium primary health care unit Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Hawassa millennium primary health care unit, Medical and health, Beyond theTesfaye Gizaw business center, Awassa.

Hawassa Millennium Primary Health Care Unit is a leading health center in Hawassa City, providing quality services to over 86,000 people both within and outside its catchment area..

ሚሊኒዬም ጤና አጠባበቅ ጣቢያ የ2018 ዓ.ም  የአስር ወር  አፈፃፀም ሪፖርት እና ሁለተኛ ዙር የ100 ቀን እቅድ ቀርበው ተገመገመ::ሚያዚያ 30/2018 ዓ/ምበመድረኩ ላይ የሀዋሳ ከተማ አ...
08/05/2026

ሚሊኒዬም ጤና አጠባበቅ ጣቢያ የ2018 ዓ.ም የአስር ወር አፈፃፀም ሪፖርት እና ሁለተኛ ዙር የ100 ቀን እቅድ ቀርበው ተገመገመ::

ሚያዚያ 30/2018 ዓ/ም

በመድረኩ ላይ የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ጤና መምሪያ የልማትና ዕቅድ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ አየሌ አረጋዊ፣ የዘርፈ-ብዙ ዳይሬክቶሬት ባለሙያ አቶ ሲሳይ ብሻሩ፣ የጤና ጣቢያው ኃላፊ አቶ ኤፍሬም ተሰማ እንዲሁም የጣቢያው ማኔጅመንት አባላትና ባለሙያዎች ተገኝተዋል።

የውይይት መድረኩን የመሩት አቶ አየሌ አረጋዊ በቀረበው ሪፖርት ዙሪያ ከባለሙያዎች ጋር ሰፊ ውይይት ካደረጉ በኋላ፣ በቀርበዉ ሪፖርት መሰረት ጡሩ አፈፃፀም የታየባቸዉ መለክያዎች(indicators) ተጠናክሮ እንድቀጠሉ እና ዝቅተኛ አፈፃፀም የተመሰገበባቸዉ ተግባራት ላይ የተያዘላቸዉ አቅጣጫ መሰረት በአጭር ግዜ ዉስጥ እንዲተገበሩ አሳስቧል።

የጤና ጣቢያው ኃላፊ አቶ ኤፍሬም ተሰማ በበኩላቸው የሁለተኛ ዙር የ100 ቀናት ዕቅድን ያቀረቡ ሲሆን፣ ዕቅዱ የአስር ወራት የአፈፃፀም መነሻ መዘጋጀቱን ጠቅሶ ዝቅተኛ ውጤት የታየባቸው ተግባራት ላይ ለውጥ ለማምጣት ልዩ ክትትልና ድጋፍ እንደሚያስፈልግም አጽንኦት ሰጥተዋል።

በመጨረሻም የክፍል አስተባባሪዎችና ፎካሎች በተቀመጠው የድርጊት መርሃ-ግብር መሰረት ክፍተቶችን በመሙላት ለተሻለ ውጤት በቁርጠኝነት ለመስራት ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል።

/ጣቢያ
#ሐዋሳ

በሚሊኒየም ጤና አጠባበቅ የ3ኛ ሩብ ዓመት የቦርድ ስብሰባ ተካሄደ:: #ሚያዚያ 29/2018 ዓ.ምበዛሬው ዕለት የሚሊኒየም ጤና አ/ጣቢያ የ2018 ዓ.ም የ3ኛ ሩብ ዓመት መደበኛ የቦርድ አባላ...
07/05/2026

በሚሊኒየም ጤና አጠባበቅ የ3ኛ ሩብ ዓመት የቦርድ ስብሰባ ተካሄደ::

#ሚያዚያ 29/2018 ዓ.ም

በዛሬው ዕለት የሚሊኒየም ጤና አ/ጣቢያ የ2018 ዓ.ም የ3ኛ ሩብ ዓመት መደበኛ የቦርድ አባላት ስብሰባ የተካሂደ ሲሆን : በመድረኩም የሩብ ዓመቱ የሥራ አፈፃፀም ሪፖርት እና በቀጣይ ትኩረት በሚሹ የተለያዩ አጀንዳዎች ቀርቦ ሰፊ ውይይት ተደርጓል።

ይህ ስብሰባ የተቋሙን አገልግሎት አሰጣጥ ይበልጥ ቀልጣፋ እና ተደራሽ ለማድረግ ያለመ ነው።


#ሀዋሳ

ሚሊኒዬም ጤና አጠባበቅ ጣቢያ PHCU acredetion እና PHFPC patient safety baseline assessment ሪፖርት ቀርቦ ተገምገመ:: /2018 ዓ.ም ሚሊኒየም ጤና ጣቢያ የ...
05/05/2026

ሚሊኒዬም ጤና አጠባበቅ ጣቢያ PHCU acredetion እና PHFPC patient safety baseline assessment ሪፖርት ቀርቦ ተገምገመ::

/2018 ዓ.ም

ሚሊኒየም ጤና ጣቢያ የጤና አገልግሎት ጥራትን ለማረጋገጥና ተገቢውን የዕውቅና ደረጃ (Accreditation) ለማግኘት የሚያስችሉ የዝግጅት ምዕራፎችን በከፍተኛ ትኩረት እያከናወነ ይገኛል። ዛሬ ሚያዝያ 27 ቀን 2018 ዓ.ም የተቋሙ ኃላፊ ፣ የኬዝ ቲም አስተባባሪዎች እና የጥራትና ቁጥጥር ባለሙያዎች በተገኙበት የሁለት ዋና ዋና ሪፎርሞች Baseline assessment ሪፖርት ቀርቦ ውይይት ተካሂዶበታል።

በመድረኩ የጤና ጣቢያው ኃላፊ አቶ ኤፍሬም ተሰማ እንደገለጹት፤ እነዚህ ሁለት ሪፎርሞች ተቋሙን ወደ አዲስ የላቀ ምዕራፍ የሚያሸጋግሩ በመሆናቸው አንስተው የተለዩ ክፍተቶች ላይ በተዘጋጀው የድርጊት መርሃ-ግብር መሰረት (Action Plan) በቁርጠኝነት እንደሚተገበር አሳስበዋል።

ሪፖርቱ ላይ ሃሳባቸውን የሰጡት የኬዝ ቲም አስተባባሪዎችም ሪፎርሞቹ ተገልጋይን ማዕከል ላደረገ አገልግሎት ለመስጠት ወሳኝ መሆናቸውን በመጥቀስ በቅንጅት እንደምሰሩ ቃል ገብተዋል።

የጥራትና ቁጥጥር ክፍል አስተባባሪ ዶ/ር ሀልቾ ኤጋታ በበኩላቸው፣ የጥራት ማረጋገጫ ስራው ቀጣይነት ባለው ክትትል (Continuous Monitoring) እና በውጤት ተኮር የግምገማ ስርአት እንደሚመራ ገልጸዋል።

አ/ጣቢያ
#ሐዋሳ

የሚሊኒየም ጤና አጠባበቅ ጣቢያ ላቦራቶሪ ክፍል የISO ስታንዳርድን ተግባራዊ ለማድረግ (ISO Implementation) እና የላቦራቶሪ አገልግሎታችንን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር ሰፊ ዝግጅት...
02/05/2026

የሚሊኒየም ጤና አጠባበቅ ጣቢያ ላቦራቶሪ ክፍል የISO ስታንዳርድን ተግባራዊ ለማድረግ (ISO Implementation) እና የላቦራቶሪ አገልግሎታችንን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር ሰፊ ዝግጅት እያደረገ ይገኛል።

ከዚህ ጋር ተያይዞ፦

✅ በቀን 23/08/2018 ዓ.ም ለላቦራቶሪ ባለሙያዎቻችን በየተሰማሩበት የሥራ ዘርፍ (Working Station) የብቃት ምዘና (Competence Assessment) ተሰጥቷል። ይህም የሙያ ብቃትን ለማረጋገጥና ጥራቱን የጠበቀ አገልግሎት ለመስጠት ትልቅ ፋይዳ አለው::

✅ በተጨማሪም በመጋቢት ወር መጨረሻ በSPHI በተደረገ የSLMTA Baseline Assessment ላቦራቶሪያችን ከመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታሎች ጋር ተመዝኖ 64% በማስመዝገብ የኮከብ 1⭐️ (Star 1⭐️) ደረጃን አግኝቷል።

ይህ ውጤት ለቀጣይ ትልቅ ስኬት መነሻችን ነው። ለዚህ ውጤት መገኘት አስተዋጽኦ ላደረጋችሁ የላቦራቶሪ ባለሙያዎቻችን እና የጤ/አ/ጣቢያችን ባለድርሻ አካላት በሙሉ ምስጋናችን ይድረሳችሁ!

#ሚሊኒየም ጤና አ/ጣቢያ
#ሐዋሳ

#ጥራትን ማረጋገጥ ቀዳሚ ተግባራችን ነው!

በሚሊኒየም ጤና ጣቢያ የ4ኛ ሩብ ዓመት የነፍሰጡር እናቶች ፎረም  አካሄደ:: #ሚያዚያ 22/2018 ዓ.ምሚሊኒየም ጤና ጣቢያ የእናቶች እና የሕፃናትን ጤና ለማሻሻል የሚያደርገውን ጥረት አካል...
30/04/2026

በሚሊኒየም ጤና ጣቢያ የ4ኛ ሩብ ዓመት የነፍሰጡር እናቶች ፎረም አካሄደ::

#ሚያዚያ 22/2018 ዓ.ም

ሚሊኒየም ጤና ጣቢያ የእናቶች እና የሕፃናትን ጤና ለማሻሻል የሚያደርገውን ጥረት አካል የሆነውን የ4ኛ ሩብ ዓመት የነፍሰጡር እናቶች የውይይት መድረክ (Forum) ዛሬ ሚያዚያ 22/2018 ዓ.ም አካሂዷል።

በመድረኩ ላይ የጤና ጣቢያው ኃላፊ አቶ ኤፍሬም ተሰማ፣ የእናቶችና ሕፃናት ክፍል አስተባባሪ ሲስተር አልማዝ አረጋታ፣ የቅድመ ወሊድ ክትትል (ANC) ክፍል ፎካል እና ባለሙያዎች በተገኙበት ከ100 በላይ እናቶች ጋር ውጤታማ ውይይት ተደርጓል።

#በመድረኩ የተዳሰሱ ዋና ዋና ነጥቦች፡

🗒️ በእርግዝና ወቅት ሊደረግ የሚገባ የአመጋገብ ሥርዓት፤

🗒️ በእርግዝና ወቅት የሚታዩ አደገኛ ምልክቶች (Danger Signs) እና ሊወሰዱ የሚገቡ ጥንቃቄዎች፤

🗒️ የግል ንጽህና አጠባበቅ እና ለወሊድ የሚደረግ ቅድመ ዝግጅት፤

🗒️ የእርስ በእርስ የልምድ ልውውጥ እና የቡድን ውይይቶች እንድሁም ከእናቶች የጥያቄ ተነስተዉ እናቶች ያነሷቸው ጥያቄዎች በባለሙያዎች ምላሽና ማበራሪያ በመስጠት የተሳካ ሁኔታ ተካሂዷል::

አ/ጣቢያ
#ሐዋሳ

ሚሊኒየም ጤ/አ/ጣቢያ 2018 ዓ/ም EPAQ 2nd Cycle BRIDGE (ጥምረት ለጥራት) የሶስተኛ ሩብ አመት ድጋፋዊ ክትትል አካሄደ።ከቀን 13/08/2018-15/08/2018 ዓ.ም በሚሊኒየ...
24/04/2026

ሚሊኒየም ጤ/አ/ጣቢያ 2018 ዓ/ም EPAQ 2nd Cycle BRIDGE (ጥምረት ለጥራት) የሶስተኛ ሩብ አመት ድጋፋዊ ክትትል አካሄደ።

ከቀን 13/08/2018-15/08/2018 ዓ.ም በሚሊኒየም ጤ/አ/ጣቢያ ጥምረት ለጥራት ትስስር ውስጥ በሚገኙት ሶስቱ ጤና ጣቢያዎች ማለትም ቡልቻ፣አዳሬ እና ጢልቴ ጤና ጣቢያዎች ላይ የሶስተኛ ሩብ ዓመት ውይይት የተካሄደው የሀገር አቀፉን ኢንሼቲቭ(EPHCG implementation, strengthen governance, leadership and accountability, improve community ownership, evidence generation and utilization and strengthen collaborative learning within EPAQ clusters and EHCRIG chapter 5(DAGU and EAPTS system) and chapter 6(BLQMS) በመከተል ድጋፋዊ ክትትል ተደርጓል ።

የዚህ ጥራት ለጥምረት አላማ ጤና ተቋማት እርስበእርስ ተደጋግፈው ጥራቱን የጠበቀ አገልግሎት እንዲሰጡ ከማድረግ ባሻገር በአንዱ ተቋም ያለውን አገልግሎት ወደ ሌላው በማስፋት በሙሉ አቅም እንዲሰሩ ለማስቻል ነው ።በመጨረሻም ሁሉም ተቋማት ላሳዩን መልካም ትብብር ከልብ የመነጨ ምስጋናችንን እናቀርባለን።
/አ/ጣቢያ
#ሀዋሳ

#𝗖𝗲𝗻𝘁𝗲𝗿 𝗼𝗳 𝗲𝘅𝗰𝗲𝗹𝗹𝗲𝗻𝗰𝗲!

የሚሊኒዬም ጤና ጣቢያ የ2018 ዓ.ም የ3ኛ ሩብ ዓመት የStaff Forum አካሄደ:: #ሚያዚያ 01/2018 ዓ.ምየሚሊኒዬም ጤና አጠባበቅ ጣቢያ የ2018 ዓ.ም የ3ኛ ሩብ ዓመት የሠራተኞች ...
09/04/2026

የሚሊኒዬም ጤና ጣቢያ የ2018 ዓ.ም የ3ኛ ሩብ ዓመት የStaff Forum አካሄደ::

#ሚያዚያ 01/2018 ዓ.ም

የሚሊኒዬም ጤና አጠባበቅ ጣቢያ የ2018 ዓ.ም የ3ኛ ሩብ ዓመት የሠራተኞች ፎረም (Staff Forum) በዛሬው ዕለት አካሂዷል።

በመድረኩ ላይ የጤና ጣቢያው ኃላፊ፣ የማኔጅመንት አባላትና የጤና ባለሙያዎች የተሳተፉ ሲሆን ፣ በዋናነት በጤና ጣቢያው የአገልግሎት አሰጣጥን በተመለከተ ሰፊ ውይይት ተደርጓል።

ተሳታፊ ባለሙያዎችም የተሻለ የሥራ አካባቢን ለመፍጠርና ለታካሚዎች ጥራት ያለው አገልግሎት ለመስጠት የሚያግዙ የተለያዩ ገንቢ ሃሳቦችን በማንሳት ተወያይተዋል።

በመጨረሻም ለተነሱ ሃሳቦች ምላሽና የቀጣይ መፍትሄ አቅጣጫዎችን ተቀምጠዉ ዉይይቱ በተሳካ ሁኔታ ተካሂዷል።

አ/ጣቢያ
#ሀዋሳ

31/03/2026
ተቀናጀ የፖሊዮ ክትባት ዘመቻ ከመጋቢት 18-21/2018 ዓ.ም ይካሄዳል፡፡
26/03/2026

ተቀናጀ የፖሊዮ ክትባት ዘመቻ ከመጋቢት 18-21/2018 ዓ.ም ይካሄዳል፡፡

"አዎ! ቲቢን ለማጥፋት እንችላለን! በመንግስት መሪነት: በሕዝባችን ኃይል!የአለም የቲቢ ቀን!"
26/03/2026

"አዎ! ቲቢን ለማጥፋት እንችላለን! በመንግስት መሪነት: በሕዝባችን ኃይል!
የአለም የቲቢ ቀን!"

አዎ! ቲቢን ለማጥፋት እንችላለን! በመንግስት መሪነት: በሕዝባችን ኃይል!
የአለም የቲቢ ቀን!



Website: moh.gov.et
Facebook: Ministry of Health,Ethiopia
Twitter: x.com/fmohealth
YouTube: youtube.com/
Tiktok: tiktok.com/
Telegram: t.me/M0H_EThiopia
LinkedIn: lnkd.in/ewFJ6VAB

 #መጋቢት 08/2018 ዓ/ም ሚሊኒየም ጤና አ/ጣቢያ ባሌሙያዎች የፍቼ ጫምበላላ በዓልን  በድምቀት አከበረ::** በዛሬው ዛሬ ዕለት የሚሊኒየም ጤና አ/ጣቢያ ባሌሙያዎች የሲዳማ ሕዝብ ዘመን ...
17/03/2026

#መጋቢት 08/2018 ዓ/ም
ሚሊኒየም ጤና አ/ጣቢያ ባሌሙያዎች የፍቼ ጫምበላላ በዓልን በድምቀት አከበረ::
**
በዛሬው ዛሬ ዕለት የሚሊኒየም ጤና አ/ጣቢያ ባሌሙያዎች የሲዳማ ሕዝብ ዘመን መለወጫ የሆነው ፍቼ ጫምባላላ በዓልን የጤና ጣቢያዉ ቦርድ አባላት እና ሌሎች ተጋባዥ እንግዶች በተገኙብት በድምቀት አከብሯል።

Address

Beyond TheTesfaye Gizaw Business Center
Awassa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Hawassa millennium primary health care unit posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share