26/11/2025
በባቲ ወረዳ አስተዳዳር የባቲ ወረዳ ጤና ጥበቃ ጽ/ቤት ከ18/3/2018 ጀምሮ ለሚካሄደው የሚኒ ካቻፕ ዘመቻ እና በወቅታዊው የማልበርግ ቨ ይረስ እንዲሁም ስለ communtiy based survillance ለጤና ጣቢያ ኃላፊዎች ፣ለኢፒያ ፎካሎች
ለፌም ፎካል፣ ፣ለጤና ኤክስቴሽንና ለወረዳ ኦፌሰሮች እና ለባለድርሻ አካላት ኦሬቴሽንና ስልጠና ሰጠ።
ህዳር 17/3/2018
በኦሮሞ ዞን በባቲ ወረዳ አስተዳዳር የባቲ ወረዳ የጤና ጥበቃ ጽ/ቤት ከ18/3/2018 ጀምሮ ለሚካሄደው የሚኒ ካቻፕ ዘመቻ እና በወቅታዊው የማልበርግ ቨ ይረስ እንዲሁም ስለ communtiy based survillance ለኢፒያ ፎካሎች፣ለፌም ፎካል ፣ለጤና ኤክስቴሽንና ለወረዳ ኦፌሰሮች እና ለባለድርሻ አካላት በተገኙበት ኦሬቴሽንና ስልጠና ተሰቷል።
በስልጠና መድረኩ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የጽ/ቤቱ ተወካይ ኃላፊ አቶ ሁሴን አብዱ እንደተናገሩት የሚኒ ካቻፕ ዘመቻ በታቀደለት ጊዜ ውስጥ እንዲጠናቀቅና ክትባት መውሰድ ያለበት አካላት በተገቢው መንገድ እንዲወስዱ ስልጠናውን በትኩረት መከታተል ይገባል ብለዋል።
አቶ ሁሴን አብዱ አክለው እንደገለጹትም የማልበርግ ቫይረስ በሽታ በሀገራችን ተከሰቶ የሰው ልጅ ሕይዎት የቀጠፈ ሲሆን እኛም የጤና ባለሙያዎች እንደወረዳችን አስፈለጊውን ጥንቃቄ በማድረግ እና ለማህበረሰባችን ስለበሽታው የግንዛቤ ፈጠራ ስራ መስራት ይገባል በማለት ገልጸዋል።