18/12/2025
አሳዛኝ የእስር ዜና
አቶ አበረ ኢሳያስ ይባላሉ ።አማራ ክልል ደቡብ ጎንደር ስማዳ ወረዳ በተስፋየ ጌታቸው መታሰቢያ ሆስፒታል ነርስ ባለሙያ ናቸው ። ትሁት ሰው አክባሪ ታታሪና ጠንካራ ሰራተኛ ናቸው ።4-4-18 ዓም በወረዳው ፖሊስ ከቤታቸው ከተቀመጡበት ታፍነው ተወስደው ታስረዋል ። ያለምንም ፍርድ 6 ቀን ሞልቷቸዋል።አሁንም እንደታሰሩ ነው ። የታሰሩበት ምክንያት 3 ወር ሙሉ ዱቲ አልተከፈለንም ይከፈለን ብለው ለሆስፒታሉ ጥያቄ ማቅረባቸውንና በተየቁት ጥያቄ በጥቆማ እንዳሳሰሩዋቸው ለጠያቂዎቻቸው ያስረዳሉ ። ወዳጀ ይህን ጨቋኝ የጤና ስርዓት ባንድ ተደራጅተህ ታግለህ መብትህን ካላስከበርክ ደክመህ የላብህን ለሰራህበት እንኳን ስትተይቅ ትታሰራለህ ።ከዚህ በላይ ጭቆና ምን ሊደርጉህ ይችላል ።አንተም ያልታሰርከው መብትህን ስላልጠየክ እንጅ በርሳቸው ቦታ ብትሆን እስር ቤት ነህ ። አሁንም የሚሰማህ ቢገኝ ድምጽ ትሆኑት ዘንድ ጥሪያችን ለሁሉም ጤና ባለሙያ እናቀርባለን ።እባካችው ድምፅ ሁኑት
https://t.me/DigitalHakim1