Dire Dawa University Teaching and Referral Hospital

Dire Dawa University Teaching and Referral Hospital Dire Dawa University Teaching and Referral Hospital (DDUTRH) is a teaching and referral hospital under Dire Dawa University.

It provides services for an estimated 5 million population in Eastern Ethiopia.

ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ማስተማሪያና ሪፈራል ሆስፒታል የክረምት በጎ ፈቃድ የህክምና አገልግሎት መስጠቱን ቀጥሏል!በዛሬው እለትም የክረምት በጎ ፈቃድ የሕክምና አገልግሎት ስራው በድሬዳዋ አስተዳደር...
26/08/2026

ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ማስተማሪያና ሪፈራል ሆስፒታል የክረምት በጎ ፈቃድ የህክምና አገልግሎት መስጠቱን ቀጥሏል!

በዛሬው እለትም የክረምት በጎ ፈቃድ የሕክምና አገልግሎት ስራው በድሬዳዋ አስተዳደር በተለያዩ አካባቢዎችና መርሃ ግብሮች ተጠናክሮ ቀጥሏል። በአሳሊሶ ክላስተር ለማህበረሰቡ ነፃ የሕክምና ምርመራ፣ የጤና ምክርና የጤና ትምህርት አገልግሎቶች ተሰጥዋል። በሌላ በኩልም፣ በቦረን የወላጅ አልባ ሕፃናት ማቋቋሚያ ማዕከል (Orphan Rehabilitation Center) የሕፃናት ሕክምና ስፔሻሊስቶች ለሕፃናት የተለያዩ የሕክምና አገልግሎቶችን ሰጥተዋል። እንዲሁም በቦረን ጤና ጣቢያ የማህፀንና ፅንስ ስፔሻሊስቶች ለእርግዝና ክትትል ለመጡ እናቶች የአልትራሳውንድ ምርመራና ሌሎች ተያያዥ የሕክምና አገልግሎቶችን ሰጥተዋል።
በምርመራው ወቅትም ተጨማሪ ሕክምና የሚያስፈልጋቸው፣ የስኳር ሕመምና የደም ግፊት ያለባቸው፣ ከእርግዝና ጋር ተያይዞ ተጨማሪ ሕክምና የሚያስፈልጋቸዉ እናቶች፣ እንዲሁም የተለያዩ ሕክምናዎች የሚያስፈልጋቸው ሕፃናቶች ወደ ሆስፒታላችን በሪፈራል ተልከው ተገቢውን ሕክምና እንዲያገኙ ተደርጓል።
የሆስፒታሉ ቺፍ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር ዶ/ር ሁሴን መሀመድ በበኩላቸው፣ የክረምቱ በጎ ፈቃድ የጤና አገልግሎቱ በማህበረሰቡ ዘንድ ትልቅ ንቅናቄና ማነቃቂያ እየፈጠረ መሆኑን ገልጸዉ፤ይህም የሕክምና ምርመራዉ በክረምት ወቅት ብቻ የሚከናወን ሳይሆን በማህበረሰቡ ዘንድ እንደ ባህል ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ገልጸዋል። በመጨረሻም በተለያዩ መርሃ ግብሮች ላይ ማህበረሰቡን በማስተባበርና ለስራዎቹ ስኬት አስተዋፅኦ ላበረከቱ ለሁሉም ባለድርሻ አካላት ምስጋናቸውን አቅርበዋል።።
ለጤናችን በጋራ እንሠራለን!!!
(ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ማስተማሪያና ሪፈራል ሆስፒታል)
ነሐሴ 20/2018 ዓ.ም

በቅርብ በሞት የተለየን የስራ ባልደረባችን የዶ/ር ያቆብ ጨመረ ለማስታወስ የሻማ ማብራት ፕሮግራም ተካሄደ።የዶ/ር ያቆብ ጨመረን ህልፈተ ሕይወት ለማስታወስ፣ የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ አመራሮች፣ የ...
23/08/2026

በቅርብ በሞት የተለየን የስራ ባልደረባችን የዶ/ር ያቆብ ጨመረ ለማስታወስ የሻማ ማብራት ፕሮግራም ተካሄደ።

የዶ/ር ያቆብ ጨመረን ህልፈተ ሕይወት ለማስታወስ፣ የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ አመራሮች፣ የሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ አመራሮች፣ የሥራ ባልደረቦቹ እንዲሁም ጎደኞቹ በተገኙበት የሻማ ማብራት ፕሮግራም በድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ማስተማሪያና ሪፈራል ሆስፒታል ተካሂዷል።

የክረምት በጎ ፈቃድ የህክምና አገልግሎት በድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ማስተማሪያና ሪፈራል ሆስፒታል ተጠናክሮ ቀጥሏል!በዛሬው እለት በድሬዳዋ አስተዳደር በአሊይ ገንዳ አሎሌ ቦታ ላይ ነጻ የህክምና ም...
22/08/2026

የክረምት በጎ ፈቃድ የህክምና አገልግሎት በድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ማስተማሪያና ሪፈራል ሆስፒታል ተጠናክሮ ቀጥሏል!
በዛሬው እለት በድሬዳዋ አስተዳደር በአሊይ ገንዳ አሎሌ ቦታ ላይ ነጻ የህክምና ምርመራ፣ የጤና ምክር አገልግሎት እንዲሁም የማህበረሰቡን ግንዛቤ ለመጨመር የጤና ትምህርት ተሰጥቷል። በበጎ ፈቃድ አገልግሎቱ ወቅት ተጨማሪ ህክምና ለሚያስፈልጋቸው ታካሚዎች ወደ ጤና ተቋም የማገናኘት (ሪፈራል) ስራ እየተሰራ ይገኛል።

የሆስፒታሉ ቺፍ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር ዶ/ር ሁሴን መሀመድ በበኩላቸው፣ የበጎ ፈቃድ የሕክምና አገልግሎቱ የማህበረሰቡን የጤና ግንዛቤና ተደራሽነት እያሳደገ መሆኑን በመግለጽ፣ በቀጣይም ሁሉንም የማህበረሰብ ክፍሎች ተደራሽ ለማድረግ በተለያዩ ቦታዎች ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል።

ለጤናችን በጋራ እንሠራለን!!!
(ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ማስተማሪያና ሪፈራል ሆስፒታል)
ነሐሴ 16/2018 ዓ.ም

21/08/2026
17/08/2026

የሐዘን መግለጫ

በድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ህክምና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ በህክምና ት/ርት ቤት ረዳት ፕሮፌሰር አና የአይን ስፔሻሊስት ሀኪም የነበሩት ዶ/ር ያቆብ ጨመረ ባደረባቸው ህመም ምክንያት በህክምና ሲረዱ ቆይተው ነሀሴ 11 ቀን 2018 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል፡፡

የድሬደዋ ዩኒቨርሲቲ በ ዶ/ር ያቆብ ጨመረ ህልፈተ ህይወት የተሰማውን ጥልቅ ሐዘን እየገለፀ ለቤተሰቡ፣ ለወዳጅ ዘመዶቹ እንዲሁም ለመላው የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ መፅናናትን ይመኛል፡፡

ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ

የጤና ሚኒስቴር ልዑካን በድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ማስተማሪያና ሪፈራል ሆስፒታል የክረምት በጎ አድራጎት ስራዎች ጉብኝት አደረጉ::በጉብኝቱም የጤና ሚኒስቴር የሜዲካል አገልግሎት መሪ ሥራ አስፈጻሚ ...
15/08/2026

የጤና ሚኒስቴር ልዑካን በድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ማስተማሪያና ሪፈራል ሆስፒታል የክረምት በጎ አድራጎት ስራዎች ጉብኝት አደረጉ::

በጉብኝቱም የጤና ሚኒስቴር የሜዲካል አገልግሎት መሪ ሥራ አስፈጻሚ ዶ/ር ኢሉባቦር ቡኖ በተለያዩ የበጎ አድራጎት ስራ ተመልክቷል። መሪ ሥራ አስፈጻሚው በዩኒቨርሲቲው ኤፍ ኤም (FM) ሬዲዮ ስቱዲዮ በመገኘት የሚሰሩ የክረምት በጎ አድራጎት ስራላይ ለማህበረሰቡ ግንዛቤ ሰጥቷል እንዲሁም በሆስፒታሉ ቅጥር ግቢ ውስጥ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ላይም ተሳትፈዋል። በተጨማሪም በበጎ አድራጎት ስራ ላይ ለነበሩ ለሕክምና ትምህርት ቤት ተማሪዎች ሙያዊ ምክርና ማበረታቻ በመስጠት ተማሪዎቹ በትምህርታቸውና በሙያዊ እድገታቸው ላይ በትኩረት እንዲሰሩ አበረታተዋል።
ልዑካን ቡድኑ በእለቱም ነፃ የሕክምና ምርመራና የጤና ምክር አገልግሎቶች፤ የችግኝ ተከላ እና የደም ልገሳ መርሃ ግብሮችንም ተዘዋዉረዉ ጎበኝቷል።
ዶ/ር ኢሉባቦር በጉብኝታቸዉም በሁሉም ዘርፍ እየተከናወኑ ያሉ የበጎ አድራጎት ስራዎች አመርቂ መሆናቸውን በመግለጽ፣ በቀጣይም እነዚህ ስራዎች ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው ገልጸዋል።
የድሬዳዋ ዩኒቨረሲቲ ማስተማሪያና ሪፈራል ሆስፒታል ቺፍ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር ዶ/ር ሁሴን መሀመድ በበኩላቸዉ፣ የተከናወኑ የበጎ አድራጎት ስራዎች የማህበረሰቡን የጤና ችግሮች በመቅረፍ ረገድ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከቱ መሆናቸውን በመግለጽ ወደፊትም አገልግሎቱ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል፡፡ በመጨረሻ ዶ/ር ሁሴን ለጤና ሚኒስቴር ልዑካን ላደረጉት ድጋፍ እና ማበረታታት ከፍተኛ ምስጋና አቅርበዋል።
ለጤናችን በጋራ እንሠራለን!!!
(ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ማስተማሪያና ሪፈራል ሆስፒታል)
ነሐሴ 09/2018 ዓ.ም

በድሬዳዋ አስተዳደር ጤና ቢሮ ኃላፊ እና በጤና ሚኒስቴር የሜዲካል አገልግሎት መሪ ሥራ አስፈጻሚ የተመራ የልዑካን ቡድን በድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ማስተማሪያና ሪፈራል ሆስፒታል ተጠናክሮ እየተሰጠ ...
14/08/2026

በድሬዳዋ አስተዳደር ጤና ቢሮ ኃላፊ እና በጤና ሚኒስቴር የሜዲካል አገልግሎት መሪ ሥራ አስፈጻሚ የተመራ የልዑካን ቡድን በድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ማስተማሪያና ሪፈራል ሆስፒታል ተጠናክሮ እየተሰጠ ያለውን የክረምት በጎ አድራጎት ሥራ ጎበኙ፡፡

የድሬዳዋ አስተዳደር ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ፅጌረዳ ክፍሌ፣ የጤና ሚኒስቴር የሜዲካል አገልግሎት መሪ ሥራ አስፈጻሚ ዶ/ር ኢሉባቦር ቡኖ፣ የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ የማስተማሪያና ሪፈራል ሆስፒታል ቺፍ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር ዶ/ር ሁሴን መሀመድ እንዲሁም ሌሎች የአስተዳደሩና የፌደራል ከፍተኛ ኃላፊዎች ሆስፒታሉ እየሰጠ ያለውን የ2018 ዓ.ም. የክረምት በጎ አድራጎት ስራዎችን ተዘዋዉረዉ ጎብኝተዋል።
በጉብኝቱ ወቅትም ልዑካኑ እየተሰጠ ያለዉ የክረምት በጎ አድራጎት ስራ የማህበረሰቡን የጤና አገልግሎት ተደራሽነትን ማሳደግ፣ በሽታዎችን ቀድሞ ለይቶ የማወቅና የመከላከል አገልግሎቶችን ማጠናከር፣ እንዲሁም የጤና ግንዛቤን በማሳደግ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን ገልጸዋል።
በተጨማሪም ሆስፒታሉ ማህበረሰብን በማገልገል፣ ማህበራዊ ኃላፊነቱን በተግባር በመወጣት እና ጥራት ያለው የጤና አገልግሎት ለማህበረሰቡ በማድረስ እያከናወነ ያለውን ተግባር ከፍተኛ አድናቆት በመስጠት ይህ ስራ በቀጣይም ተጠናክሮ እንዲቀጥል አቅጣጫ ተሰጥቷል።
ለጤናችን በጋራ እንሠራለን!!!
(ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ማስተማሪያና ሪፈራል ሆስፒታል)
ነሐሴ 08/2018 ዓ.ም

በድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ማስተማሪያና ሪፈራል ሆስፒታል የክረምት በጎ አድራጎት ሥራዎች ተጠናክረው ቀጥለዋል!*በድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ማስተማሪያና ሪፈራል ሆስፒታል የ2018 ዓ.ም. የክረምት በጎ አድ...
08/08/2026

በድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ማስተማሪያና ሪፈራል ሆስፒታል የክረምት በጎ አድራጎት ሥራዎች ተጠናክረው ቀጥለዋል!
*
በድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ማስተማሪያና ሪፈራል ሆስፒታል የ2018 ዓ.ም. የክረምት በጎ አድራጎት መርሃ ግብሮች በተለያዩ አካባቢዎች በሰፊው እየተከናወኑ ይገኛሉ። መርሃ ግብሮቹ የማኅበረሰቡን ጤና፣ ደኅንነትና የአካባቢ ጥበቃን ለማሻሻል የሚያስችሉ የተለያዩ ተግባራት በቅንጅት እየተፈጸሙ ይገኛሉ። በመርሃ ግብሩ ማዕቀፍ ውስጥ ነፃ የሕክምና እና የጤና ምክር አገልግሎት፣ የችግኝ ተከላ፣ እንዲሁም የደም ልገሳ መርሃ ግብሮች በስፋት እየተከናወኑ ይገኛሉ።
በዚህም መሰረት የበጎ አድራጎት እና የጤና አገልግሎት መርሀ- ግብሮችን በማስፋፋት ማኅበረሰቡን ማገልገሉን እንደሚቀጥልም የሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅና ሆስፒታል ቺፍ ኤክስኪዮቲቭ ዳይሬክተር ዶ/ር ሁሴን መሀመድ መልዕክት አስተላልፏል።
*
ለጤናችን በጋራ እንሠራለን !!!
(ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ማስተማሪያና ሪፈራል ሆስፒታል)
ነሐሴ 02/2018 ዓ.ም

Address

Dire Dawa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Dire Dawa University Teaching and Referral Hospital posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Dire Dawa University Teaching and Referral Hospital:

Shortcuts

Share