19/03/2026
የድሬዳዋ አስተዳደር ቀልዓድ ጤና ጣቢያ ኃላፊ ሲ/ር ደገን ኢሴ 1447ኛው የኢድ አልፈጥር በአል አስመልክቶ ያስተላለፉት መልዕክት
ውድ የቀልዓድ ጤና ጣቢያ ሠራተኞች፣ አጠቃላይ የወረዳው የሥራ ኃላፊዎች እና የወረዳው ማህበረሰብ እንኳን ለ1445ኛው የኢድ አል-ፊጥር ረመዳን በዓል፥ በሰላም እና በጤና አደረሰን/አደረሳችሁ።
ያሳለፍነው የረመዳን ጾም ወር ፥ ዋነኛ ሥርዓቶች ከሆኑት የፀሎት እና የስግደት መንፈሳዊ ተግባራት በተጨማሪ ፥ በብዙ የበረከት ሥራዎች የታጀበ ወር ነበር።
የነገዋ የኢድ ዕለት፥ በረመዳን የጾም ወር የፈፀምናቸውን የአንድነት፥ የእዝነት፥ የመረዳዳት እና ሌሎች በርካታ መልካም እሴቶች አጠንክረን፥ በቀጣይ የዕለት ተዕለት ኑሯችን ውስጥ ለማስቀጠል ለራሳችን ቃል የምንገባበት ልዩ ቀን ናት።
'ረመዳን ሙባረክ' ተባብለን የጀመርነውን የጾም፥ ፀሎት እና ስግደት ወር በሰላም እንድንጨረስ ለረዳን ፈጣሪ ምስጋና እያቀረብኩ፥ ለመላው የእስልምና እምነት ተከታይ ወገኖቼ ይህ በዓል የፍቅር፥ የመረዳዳት እና የአብሮነት እንዲሆንላችሁ እመኛለሁ።
ኢድ ሙባረክ