fami

fami ኩሩ የኢትዮጵያ ልጅ 🇪🇹🇪🇹

በሐረሪ ክልል 7ኛው አገራዊ ምርጫ ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የዝግጅት ስራዎች እየተከናወኑ ይገኛል በሐረሪ ክልል 7ኛው አገራዊ ምርጫ ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑ የክልሉ...
06/05/2026

በሐረሪ ክልል 7ኛው አገራዊ ምርጫ ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የዝግጅት ስራዎች እየተከናወኑ ይገኛል

በሐረሪ ክልል 7ኛው አገራዊ ምርጫ ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑ የክልሉ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ ገለጸ

የሀረሪ ክልል ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ አቶ ቶፊቅ መሀመድ እንደገለጹት የማህበረሰቡን ተሳትፎ በማሳደግ ሰላምን ማጠናከር ያስቻሉ ስራዎች ተከናውነዋል።

እንዲሁም በክልሉ የፀጥታ መዋቅር ከማጠናከርና የፀጥታ ስጋት ከማስወገድ አንፃር በትኩረት ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል።

የጸጥታ ሃይሉ፣ ማህበረሰቡና የሰላም አደረጃጀቶችን ባሳተፈ መልኩ የሚከናወነው የሰላምና የጸጥታ ስራዎች ወደ ተሻለ ደረጃ ማድረስ መቻሉን ተናግረዋል።

በክልሉ በአሁኑ ወቅትም አወንታዊ ሰላም መገኘቱንና ይህንንም ዘላቂ ከማድረግ አንጻር የተቀናጀ ስራ እየተከናወነ ይገኛል ብለዋል።

በተለይ በክልሉ ጸጥታ መዋቅሩ ላይ የተከናወኑት የሪፎርም ስራዎች ለተገኘው ወጤት አስተዋጽዎ ማድረጉን አብራርተዋል።

እንዲሁም ህዝቡን በሰላምና ጸጥታ ስራዎች ላይ በማሳተፍ የሰላሙ ባለቤት እንዲሆኑ በማስቻል ረገድ የተከናወኑት ስራዎችም ውጤት ማስገኝቱን ገልጸዋል።

በዚህም በክልሉ ኮንትሮባንድን፣ ህገወጥ የመሬት ወረራና ግንባት፣ ህገወጥ ንግድና የነዳጅ ሽያጭ በመከላከልና በድርጊቱ የተሰማሩ አካላትን በቁጥጥር ስር እንዲውሉ መደረጉንም አንስተዋል።

በክልሉ 7ኛው አገራዊ ምርጫ በቅድመም ሆነ በምርጫ ወቅትና ከምርጫ በኋላ ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ህዝቡን ያሳተፈ ስራዎች በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን አንስተዋል።

የህዝብን ተሳትፎ በማጠናከር የተጀመሩ የሰላምና ጸጥታ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አቶ ቶፊቅ አክለው ተናግረዋል።

ኅብረ ብሔራዊ አንድነት፦ ለሀገረ መንግሥት ፅናት!ኅብረ ብሔራዊ አንድነት ማለት ከሁለት ፅንፎች የተላቀቀ ቀመር ነው። “ለኅብርነት ቦታ ከማይሰጥ አንድነት” እና “ለአንድነት ቦታ ከማይሰጥ ኅብ...
03/05/2026

ኅብረ ብሔራዊ አንድነት፦ ለሀገረ መንግሥት ፅናት!

ኅብረ ብሔራዊ አንድነት ማለት ከሁለት ፅንፎች የተላቀቀ ቀመር ነው።

“ለኅብርነት ቦታ ከማይሰጥ አንድነት” እና “ለአንድነት ቦታ ከማይሰጥ ኅብርነት” የተላቀቀ፡፡

ኅብረ ብሔራዊነት ሀገራዊ መልክ፣ ከአንድነት ጋር ሊጋጭ የማይችል መሆኑን ዕውቅና ይሰጣል፡፡

በሌላ በኩል ደግሞ ወደ ፅንፍ ወጥቶ ሀገራዊ አንድነትን አደጋ ውስጥ እንዲጥል አይፈቅድም፡፡

እንዲሁም ሀገራዊ አንድነት ስንል - አንድ የፖለቲካና የኢኮኖሚ ማኅበረሰብ ለመገንባት በሚያስችሉ ዕሤቶች ላይ የተመሠረተ፣ ለኅብረ ብሔራዊነት ዕውቅና የሰጠ እና በወል ትርክት ላይ የተገነባ ነው፡፡

ብልፅግና ይሄንን ሀገር የሚያጸና ዕሳቤ መሬት ላይ በሚገባ በማውረድ፣ የሀገረ መንግሥቱን ፅናት ለመፍጠር ይሠራል፡፡

ኅብረ ብሔራዊ አንድነትን ለማፅናት በሚከተሉት ዐበይት ጉዳዮች ላይ ፓርቲያችን አበክሮና አጠናክሮ ይሠራል።




የሀረሪ እና የድሬዳዋ የህዝብ ለህዝብ ግንኙነቱ ለ7ኛው ምርጫ ስኬት መሰረት ነው" :- አቶ ኦርዲን በድሪየሀረሪ እና የድሬዳዋ የህዝብ ለህዝብ ግንኙነቱ ለ7ኛው ምርጫ ስኬት መሰረት ነው" ሲሉ...
03/05/2026

የሀረሪ እና የድሬዳዋ የህዝብ ለህዝብ ግንኙነቱ ለ7ኛው ምርጫ ስኬት መሰረት ነው" :- አቶ ኦርዲን በድሪ

የሀረሪ እና የድሬዳዋ የህዝብ ለህዝብ ግንኙነቱ ለ7ኛው ምርጫ ስኬት መሰረት ነው" ሲሉ የሀረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳደር አቶ ኦርዲን በድሪ ገለፁ

በሀረሪ ክልል እና በድሬዳዋ አስተዳደር አመራሮችና ህዝቦች መካከል ያለውን ታሪካዊ አብሮነትና ወንድማማችነት ይበልጥ ለማጠናከር ያለመ የወዳጅነት ስፖርታዊ ውድድር በታሪካዊቷ የሀረር ከተማ በደመቀ ሁኔታ በመካሄድ ላይ ይገኛል።

መርሐ ግብሩ ላይ የሀረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ እንደገለፁት፤ መሰል መድረኮች በሁለቱ ጎረቤታማ ህዝቦች መካከል ያለውን "የመደመር" እሴት በተግባር የሚያሳዩ ናቸው።

ይህ ወንድማማችነትና አንድነት ለአከባቢው ሰላም መረጋገጥና ለጋራ ልማት አጋርነት መጎልበት የማይተካ ፋይዳ እንዳለውም አስገንዝበዋል።

ርዕሰ መስተዳድሩ አክለውም፣ ይህ ስፖርታዊ መድረክ እየተቃረበ ለሚገኘው 7ኛው ሀገራዊና ክልላዊ ምርጫ ትልቅ ግብዓት መሆኑን ገልጸዋል።

"ጠንካራ የህዝብ ለህዝብ ትስስር መኖሩ ምርጫው ሰላማዊ፣ ዲሞክራሲያዊና ተአማኒ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ምቹ ሁኔታን ይፈጥራል" ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል።

የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሀር በበኩላቸው፤ መርሐ-ግብሩ በሁለቱ ህዝቦች መካከል ከጥንት ጀምሮ የዘለቀውን ጥልቅ ታሪካዊና ባህላዊ ትስስር ይበልጥ ለማነቃቃት የታለመ መሆኑን ገልፀዋል።

መሰል ስፖርታዊ ውድድሮች ማህበራዊ መስተጋብርን ወደ ላቀ ደረጃ በማሸጋገር ረገድ ከፍተኛ ሚና እንደሚጫወቱም ጠቁመዋል።

ከንቲባው አያይዘውም፣ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታው እንዲጎለበትና ምርጫው በሰላም ተጀምሮ በስኬት እንዲጠናቀቅ የሁለቱ አካባቢዎች ህዝቦች ያላቸውን አብሮነት አጠናክረው እንዲቀጥሉ አሳስበዋል።

በልዩ ልዩ ስፖርታዊ ውድድሮች የታጀበው ይህ የወዳጅነት መድረክ፣ በሁለቱ ህዝቦች መካከል ያለውን "የእህትማማችነት" መንፈስ ባረጋገጠ መልኩ ቀጥሎ ውሏል።

#አንድነት፦ስፖርት ለወንድማማችነት።
#ልማት፦ የጎረቤታማ አካባቢዎች የጋራ እድገት።
#ዴሞክራሲ፦ሰላማዊ ምርጫን በአብሮነት ማረጋገጥ።

03/05/2026
03/05/2026
03/05/2026

ሐረር & ድሬ ደዋ ይለያሉ 🙏❤️🙏

Address

Ethiopian
Harar

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when fami posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share