የኣሪ ዞን ጤና መምሪያ Aari Zone Health Department

  • Home
  • Ethiopia
  • Jinka
  • የኣሪ ዞን ጤና መምሪያ Aari Zone Health Department

የኣሪ ዞን ጤና መምሪያ Aari Zone Health Department የዜጎች ጤና ለሀገር ብልጽግና በሚል መሪህ የጤና ሥርዓቱን አጠናክሮ ማስቀጠል

ወባን ለመከላከል ማህበረሰቡ ተሳትፎ እያደረገ ይገኛል ጂንካ_ግንቦት 12/2018(ኣዞጤመ)በኣሪ ዞን የተከሰተውን የወባ ወረርሽኝ ለመከላከል በማህበረሰቡ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት በምስል ጂን...
20/05/2026

ወባን ለመከላከል ማህበረሰቡ ተሳትፎ እያደረገ ይገኛል

ጂንካ_ግንቦት 12/2018(ኣዞጤመ)

በኣሪ ዞን የተከሰተውን የወባ ወረርሽኝ ለመከላከል በማህበረሰቡ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት በምስል ጂንካ ከተማ ፣ ባካዳውላ፣ ጋዜር ከተማ እና ደቡብ ኣሪ

የዜጎች ጤና ለሀገር ብልጽግና‼️

የኣሪ ዞን ጤና መምሪያ ገጾች Follow በማድረግ እንድከታተሉን እንጋብዛለን ።

ተለግራም https://t.me/AariZoneHealthDepartment

tiktok.com/

https://www.facebook.com/profile.php?id=61565064929502

20/05/2026
የኣሪ ዞን ጤና መምሪያ በGavi በጀት ድጋፍ እየተሰራ ያለውን የተቀናጀ ዘመቻ በበይነ መረብ መገምገሙን ገለጿልጂንካ_ግንቦት 11/2018(ኣዞጤመ)በኣሪ ዞን ሥር ባሉ ሁሉም መዋቅሮች እየተከና...
19/05/2026

የኣሪ ዞን ጤና መምሪያ በGavi በጀት ድጋፍ እየተሰራ ያለውን የተቀናጀ ዘመቻ በበይነ መረብ መገምገሙን ገለጿል

ጂንካ_ግንቦት 11/2018(ኣዞጤመ)

በኣሪ ዞን ሥር ባሉ ሁሉም መዋቅሮች እየተከናወነ የሚገኘውን የተቀናጀ የእናቶችና ሕጻናት ዳይሬክተሩ አቶ ይሁን ጋሎ የበይነ መረብ ውይይቱን የመሩት ሲሆን የhead count , ዜሮ ዶዝ፣ under vaccinated እንድሁም የምግብ ኦጥረት ልየታ እና የHPv ክትባት ስራዎችን አፈጻጸም መገምገም መቻሉን ገልጸዋል ።

ከወረዳዎቹ አስተያየት እና ጥያቄ ተነስቶ ምላሽ እና ማብራርያ ተሰጥቶባቸዋል ።

የዜጎች ጤና ለሀገር ብልጽግና‼️

የኣሪ ዞን ጤና መምሪያ ገጾች Follow በማድረግ እንድከታተሉን እንጋብዛለን ።

ተለግራም https://t.me/AariZoneHealthDepartment

tiktok.com/

https://www.facebook.com/profile.php?id=61565064929502

19/05/2026
19/05/2026
የወባ ወረርሽኝ መከላከል እና የመቆጣጠር ሥራው ተጠናክሮ መቀጠሉ ተገለፀ ።ጂንካ_ግንቦት 10/2018(ኣዞጤመ)የኣሪ ዞን ጤና መምሪያ የወባ በሽታ ወረርሽኝን ለመከላከል እና ለመቆጣጠር በባካ ...
18/05/2026

የወባ ወረርሽኝ መከላከል እና የመቆጣጠር ሥራው ተጠናክሮ መቀጠሉ ተገለፀ ።

ጂንካ_ግንቦት 10/2018(ኣዞጤመ)

የኣሪ ዞን ጤና መምሪያ የወባ በሽታ ወረርሽኝን ለመከላከል እና ለመቆጣጠር በባካ ዳውላ ኣሪ ወረዳ በግስተ ቀበሌ ለህሙማን በዘመቻ የወባ ሕክምና መሥጠት የቸቻለ ሲሆን በዝህ አግልግሎት ማህበረሰቡ በአቅራቢያቸው አግልግሎቱ መጀመሩ ከአላስፈላጊ ወጪ የታደጋቸው መሆኑን በመግለጽ ቀጣይነት እንድኖረውና በየቤቱ በወባ የታመሙ መኖራቸውን በስፍራው የዞኑ ደጋፊዎች እና የወረዳው ማናጅመንት ተገኝተው ምልከታ አድረገዋል።

በቀጣይም መሠራት ያለባቸው ተግባራት በመንግስት የኬምካል ሪጭት እንድሚያስፈልግ እና ከማህበረሰቡ ደግሞ የአካባቢ ቁጥጥር ሥራዎች ተጠናክረው እንድቀጥሉ እና በጋራ ከተቀናጀን ወረርሽኙን መከላከል እንችላለን ያሉት የወረዳው ጤና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አባቴ ባማይ ናቸው።

በወረዳው ከዛሬ ጀምሮ ከፍተኛ የወባ ጫና ባለባቸው ቀበሌያት በዘመቻ መልኩ የምርመራ እና ሕክምና በጤና ኬላ እና በተመረጡ ጊዜያዊ ጣቢያዎች የሚከናወን ሲሆን በዝህም ማህበረሰቡ በአቅራቢያቸው ባሉ ጤና ኬላዎች እና ጊዜያዊ ጣቢያዎች በመገኘት በነጻ የወባ ምርመራ እና ህክምና አግልግሎት እንድያገኙ እና በወባ መከላከል የሚደረገውን ሥራ መንግስታዊና አጋር አካላት አስፈላጊውን ደጋፍ እንድያደርጉ ጥሪ ቀርቧል።

በደቡብ ኣሪ ወረዳ የተመደቡ የዞን ደጋፊ ባለሙያዎች በሜፀር ቀበሌ የአጎበር አጠቃቀም እና አካባቢ ቁጥጥር ሥራዎች ምልከታ ያደረጉ ሲሆን በቀሪ መዋቅር የመከላከል ሥራዎች ትኩረት እንደሰጠው ተመላክቷል።

የዜጎች ጤና ለሀገር ብልጽግና‼️

የኣሪ ዞን ጤና መምሪያ ገጾች Follow በማድረግ እንድትከታተሉን እንጋብዛለን ።

ተለግራም https://t.me/AariZoneHealthDepartment

tiktok.com/

https://www.facebook.com/profile.php?id=61565064929502

በኣሪ ዞን የተከሰተውን የወባ ወረርሽኝ ለመከከላከል የንቅናቄ መድረኮች እየተከናወኑ ይገኛል ጂንካ_ግንቦት 8/2018 (ኣዞጤመ)  ወረርሽኙን ለመከላከል በጂንካ ከተማ እና በጋዜር ከተማ የንቅ...
16/05/2026

በኣሪ ዞን የተከሰተውን የወባ ወረርሽኝ ለመከከላከል የንቅናቄ መድረኮች እየተከናወኑ ይገኛል
ጂንካ_ግንቦት 8/2018 (ኣዞጤመ)

ወረርሽኙን ለመከላከል በጂንካ ከተማ እና በጋዜር ከተማ የንቅናቄ መድረክ የተካሄደ ሲሆን በመድረኮቹም በመንግስት ዋና ተጠሪና የጂንካ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ግርማ ገብረና የተከበሩ የምክር ቤት አፈጉባኤ እንድሁም የከተማው አመራር እና የቀበሌ ሊቀመንቤሮች ተገኝተዋል።

የጤና ኤክስቴንሽን ሠራተኞች እና የጤና ጽ/ቤት ባለሙያዎች ተሳትፈውበታል ።

የዜጎች ጤና ለሀገር ብልጽግና

የኣሪ ዞን ጤና መምሪያ የwk19/2026 PHEOC መገምገሙን እና የወባ ወረርሽኝን ለመግታት ድጋፍና ክትትል ቡድን ማሰማራቱን አስታወቀ፣ጂንካ_ግንቦት 7/2018 ዓ/ም (ኣዞጤመ)  በ19ኛ ሳ...
15/05/2026

የኣሪ ዞን ጤና መምሪያ የwk19/2026 PHEOC መገምገሙን እና የወባ ወረርሽኝን ለመግታት ድጋፍና ክትትል ቡድን ማሰማራቱን አስታወቀ፣

ጂንካ_ግንቦት 7/2018 ዓ/ም (ኣዞጤመ)

በ19ኛ ሳምንት PHEOC በተገመገመበት ወቅት የወባ በሽታ 2429 ሰው በበሽታው ተይዘው የሕክምና አግልግሎት ማግኘታቸው ተገምግሟል።

ከፍተኛ የወባ ጫና ያለባቸው መዋቅሮችን በመለየት ልዩ ድጋፍና ክትትል ቡድን በማዋቀር ወደስራ የተገባ ሲሆን በጂንካ ከተማ ፣ በደቡብ ኣሪ ፣ በባካ ዳውላ እና በጋዜር ከተማ ጫናው ከፍ ማለቱን በማንሳት በእነዝሁም ወረዳዎች የተመደቡ የድጋፍ ቡድኖች ከዛሬ ጀምሮ ትግበራ መጀመራቸውን አመላክተዋል ። በቀሪ መዋቅሮችም የመከላከያ መንገዶች እንድተገበሩ እና የታመሙት የፈወቀስ ሕክምና እንድያገኙ በሁሉም መዋቅር በትኩረት እንድሰራ ያሳሰቡት የኣሪ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ በድሉ ባጊማስ ነቸው።

በተጨማሪም የባካዳውላ ወረዳ የዞኑ ደጋፊዎች ወደ ወረዳው እየተንቀሳቀሱ ሲሆን በዛሬው ውሎ በጤና ጽ/ቤት ማኔጅመንት ጋር በመወያየት በወባማ ቀበሌዎች የጽ/ቤት ደጋፊዎች በመመደብ እና ከጤና ጣቢያው ባለሙያዎች ጋር በመተባበር በቀጣይ 1 ሳምንት በዘመቻ መልኩ የወባ መከላከል ንቅናቄ እንድሰራ በመግባባት ተጠናቋል ።

በመጨረሻም በወረዳው አስተዳደር በመገኘት ከባካ ዳውላ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ መሠረት ቦጋለ ጋር የዞኑ ደጋፊዎች የመከሩ ሲሆን በመጨረሻም በሚከተሉት ጉዳዮች ላይ ከስምምነት ተደርሷል ።

1, በወረዳው ባሉ ወባማ ቀበሌዎች ከሚገኙ የቀበሌ አስተዳዳሪዎች እና የወረዳ ደጋፊዎች ጋር በመሆን የንቅናቄ መድረክ ግንቦት 10/2018 እንደሚደረግ

2, ዘመቻው በወረዳ ኮማንድ ፖስት በየቀኑ እንድገመገም

3 በቀበሌ ደረጃ የንቅናቄ ሥራዎች በልዩ ዲስፒሊን እንድመራ እና

4, ለሕሙማን የፈውስ ሕክምና ለመስጠት አስፈላጊ ግብዓቶች እንድሟሉ በአስተዳደር ደረጃ በተቻለው መጠን አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርጉ የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ ገልጸዋል ።

በመጨረሻም ሁሉም የሕብረተሰብ ክፍል የወባ በሽታ ወረርሽኝን ለመከላከል በትኩረት የራሱንና አካባቢውን ጽድት በመጠበቅ ለወባ ትንኝ መራቢያ ምቹ ቦታዎችን እንድያስወግዱ አቶ መሠረት ቦጋሌ የባካ ዳውላ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ ጥሪ በማስተላለፍ ውይይቱን አጠቃለዋል ።

በሽታው በወረዳው ስር ከምገኙ ከ12ቱ ቀበለያት በግስቴ፣ ካይሣ፣ ባያሞር፣ አርክሻ ፣ አሊ እና ጌዛ ቀበሌዎች ላይ በወረርሽኝ መልክ መከሰቱን የጠቆሙት የወረዳው ጤና ጽ/ቤት ኃላፊው አቶ አባቴ ባማይ ናቸው።

// የዜጎች ጤና ለሀገር ብልጽግና//

የኣሪ ዞን ጤና መምሪያ ሚከተሉትን ገጾች Follow በማድረግ እንድከታተሉን እንጋብዛለን ።

ተለግራም https://t.me/AariZoneHealthDepartment

tiktok.com/

https://www.facebook.com/profile.php?id=61565064929502

የኣሪ ዞን ጤና መምሪያ የ2018 በጄት ዓመት የ10 ወር የአጠቃላይ አፈጻጸም በመምሪያ ደረጃ መገምገሙን አስተውቋል ።ጂንካ_ግንቦት 5/2018 (ኣዞጤመ)   አጠቃላይ የሁሉም ዳይሬክተሮች ዕቅ...
13/05/2026

የኣሪ ዞን ጤና መምሪያ የ2018 በጄት ዓመት የ10 ወር የአጠቃላይ አፈጻጸም በመምሪያ ደረጃ መገምገሙን አስተውቋል ።

ጂንካ_ግንቦት 5/2018 (ኣዞጤመ)

አጠቃላይ የሁሉም ዳይሬክተሮች ዕቅድ አፈጻጸም በልማት ዕቅድና ኢኮኖሚ አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ቡድን መሪ አቶ ኢንድርያስ ቦጮለ በኩል በስፋት ቀርቧል።

በቀረበው አፈጻጸም መሠረት በእናቶች እና ሕጻናት ፣ በበሽታ መከላከል እንድሁም በሕክምና አግልግሎት ዘርፍ እንድሁም በድንገተኛ አደጋ ክስተቶች መከላከል እና መቆጣጠር ተግባራት በቀጣይ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እንድሰራ ተመላክቷል ።

በመጨረሻም ወቅታዊ እና ታዓማኒነት ያላቸውን የመረጃ ልውውጥ ሥርዓቱ አሁን ካለበት ጥራቱን በጠበቀ መልኩ እንድናከናወንና ሁሉም ዳይሬክቶሬት ከታችኛው የወረዳ መዋቅር ባለሙያዎች ጋር በየወሩ አፈጻጸሞች እየተገመገሙ ግብረመልስ እየተሰጠ ማስተካከያ እንድደረግ እና የወባ በሽታ ወረርሽኝን ለመከላከል እና ለመቆጣጠር ሁሉም በጋራ በመተባበር ካልተሰራ የከፋ ጉዳት ከማስከተሉ በፍት ቅንጅታዊ አሰራር በመዘርጋት ወባ ሥራ በዘመቻ እንድሰራ የጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ በዲሉ ባጊማስ በመግለፅ መድረኩን አጠቃለዋል ።

በመድረኩ የመምሪያው ማነጅመንት አካላት ተሳትፈዋል

የዜጎች ጤና ለሀገር ብልጽግና‼️

የኣሪ ዞን ጤና መምሪያ ገጾችን Follow በማድረግ እንድከታተሉን እንጋብዛለን ።

ተለግራም https://t.me/AariZoneHealthDepartment

tiktok.com/

https://www.facebook.com/profile.php?id=61565064929502

በሁሉም ወረዳዎች እና ከተማ አስተዳደሮች የወባ መከላከል ንቅናቄ እንድካሄድ የኣሪ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ በዲሉ ባጊማስ መልእክት አስተላልፈዋል ።ጂንካ_ሚያዝያ 30/2018 (ኣዞጤመ) ይ...
08/05/2026

በሁሉም ወረዳዎች እና ከተማ አስተዳደሮች የወባ መከላከል ንቅናቄ እንድካሄድ የኣሪ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ በዲሉ ባጊማስ መልእክት አስተላልፈዋል ።

ጂንካ_ሚያዝያ 30/2018 (ኣዞጤመ)

ይህም የተላለፈው የ2026/18ኛ ሳምንት EOC በተገመገመበት ወቅት ሲሆን 2438 ሰው በሳምንቱ በጤና ተቋማት የታከሙ መሆኑንና ይህም በባለፈው ሳምንት ከነበረው 1805 ሰው በ633/34% በሽታው በዞናችን መጨመሩ የተገለፀ ሲሆን ይህም ከወቅቱ የዝናብ ሁነታ ጋር ተደምሮ በማህበረሰቡ ላይ ስጋት ደቅኗል።

ለዝህ ወባ ወረርሽኝ በተለይም በአንደኛነት ጂንካ ከተማ 1265 /55% ታማሚዎችን በመያዝ ከሌሎች ወረዳዎች ከፍተኛ ጫና ያለበት ሲሆን በሁለተኛ ደግሞ የደቡብ ኣሪ ወረዳ 488 ሰው የታመመበት መዋቅር መሆኑ ተመላክቷል።

ከአካባቢ ቁጥጥር ስራው በተጨማሪም ማህበረሰቡ በእጁ ያለውን የአልጋ አጎበር በአግባቡ በመጠቀም እራሱንና የቤተሰቡን ሕይወት መጠበቅ እንዳለበት የዞኑ ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ በዲሉ ባጊማስ አሳስበዋል ።

በተጨማሪም በየደረጃው ያለው የጤና መዋቅር ከአስተዳደር አካላት ጋር በመቀናጀት የወባ ንቅናቄ መድረኮች ተፈጥረው የአካባቢ ቁጥጥር ሥራዎች በዘመቻ መልኩ እንድሰሩ ጤና መምሪያው አስፈላጊውን ድጋፍ እንደምያደርግ በመግለፅ መድረኩን አጠቃለዋል ።

ለሎች በሳምንቱ የተከናወኑ ተግባራት ቀርበው በመገምገም ግብረ መልስ ተሰጥቶባቸዋል ።

የዜጎች ጤና ለሀገር ብልጽግና‼️

የኣሪ ዞን ጤና መምሪያ ሚከተሉትን ገጾች Follow በማድረግ እንድከታተሉን እንጋብዛለን ።

ተለግራም https://t.me/AariZoneHealthDepartment

tiktok.com/

https://www.facebook.com/profile.php?id=61565064929502

በኣሪ ዞን  የደቡብ ኣሪ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት  ም/ኃላፊ አቶ ልዩ ካማይ እና የወረዳው ድንገተኛ አ/አስሳ ቅኝት ባለሙያ  በጋራ በመሆን በሜፀር ክላስተር  ያለውን የወባ ጫና በሜፀር ቀበሌ ድረ...
05/05/2026

በኣሪ ዞን የደቡብ ኣሪ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት ም/ኃላፊ አቶ ልዩ ካማይ እና የወረዳው ድንገተኛ አ/አስሳ ቅኝት ባለሙያ በጋራ በመሆን በሜፀር ክላስተር ያለውን የወባ ጫና በሜፀር ቀበሌ ድረስ በመሄድ ያለበትን ደረጃ ምልከታ አድርገዋል ።

ጂንካ_ሚያዝያ 27/2018

በወረዳው በረካ ክላስተረ ጨለጎድ ቀበሌ እና ሜፀር ክላስተር ሜፀር ቀበሌና ሽሽር ቀበሌ ከፍተኛ ወባ ጫና መኖሩ ተገልጿል ።

በወረዳው ጤና ጽ/ቤት ም/ ኃላፊ አቶ ልዩ ካማይ የተመራ ቡድን ሜፀር ቀበሌ የወባ ሥራዎች ያለበትን ደረጃ እና የአከባቢ ቁጥጥር ሥራዎችን ተመልክቶ አስፈላጊውን ሙያዊ ድጋፍ አድርገዋል ።

በተጨማሪም በከተማው ውስጥ ቤት ለቤት እና በጤና ኤክስተንሽን አማካይነት ቋም የወባ መራቢያ ቦታዎችን የተለዩ ብዛት አራት ስሆን አንዱን በአካል ዜሌት ህብርት በመጎበኝት ድጋፋቸውን አጠናቀዋል።

መረጃው የደቡብ ኣሪ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት ነው

የዜጎች ጤና ለሀገር ብልጽግና
የኣሪ ዞን ጤና መምሪያ

Address

South
Jinka

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የኣሪ ዞን ጤና መምሪያ Aari Zone Health Department posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share