30/09/2022
Abortion
በኢትዮጵያ ውርጃ የሚፈቀድባቸው 5 ምክንያቶች
🖲 የጤና ባለሞያዎች ለሁለቱም ፃታዎች የእርግዝና መከላከያ መንገዶችን እንዲጠቀሙ የሚመክሩት ያለምክኒያት አይደለም
🖲ጥንቃቄ በጎደለው ግንኙነት ምክኒያት ያልታቀደ እርግዝና ሲያጋጥም የአብዛኞች ውሳኔ እንደምታቁት ህገወጥ ወርጃ ነው።
🖲በሀገራችን ውስጥ ውርጃ የሚፈቀድባቸው 5 መንገዶች ብቻ ናቸው።
👉1. በመደፈር እና በዘመድ መካከል ግንኙነት የተፈጠረ አርግዝና ከሆነ
👉2. የእርግዝናው መቀጠል የእናትየዋን ህይወት የሚያጨናግፍ ከሆነ
👉3. ፅንሱ ሊድን የማይችል የአካል ጉድለት ካለው
👉4. እናትየዋ ለአቅመ ሄዋን ያልደረሰች ወይም የአእምሮ በሽታ እና የአካል ጉድለት ተጠቂ ከሆነች እንዲሁም
👉5. ግዜ በማይሰጥ ድንገተኛ አደጋ እና በበሽታ ምክኒያት አፋጣኝ ህክምና የሚደረግ ከሆነ። ውርጃ በህግ ይፈቀዳል
🖲 ከዚህ ውጪ የሚደረጉ ውርጃዎች ፣በፍርድ ቤት ውሳኔ ፣በባለሞያው እና ፈቅዳ ውርጃን የምታከናውነው እርጉዝ ሴት ላይ በወንጀል ህግ ያስቀጣል
🖲አሳሳቢው ሁኔታ በህግ ተጠያቂ መሆን ብቻ ሳይሆን ፡ አንዳንዴ ከውርጃ በኋላ የሚያጋጥም የጤና ችግር፣ ከግዜ በኋላ የሚፀፅት የእድሜ ልክ ጠባሳንም ትቶ ሊያልፍ ይችላል።
ለተጨማሪ ጤና መረጃ የቴሌግራም ቻላናች ይቀላቀሉ
https://t.me/+UbojqWNhpSZ01_-m