Yirgalem Primary Health Care Unit

Yirgalem Primary Health Care Unit Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Yirgalem Primary Health Care Unit, Medical and health, Sidama Yirgalem, Yirgalem.

የጨረታ ማስታወቂያ የይ/ዓለም ከተማ ጤና ጣቢያ የተለያየ የአሮጌ/ ያገለገሉ ንብረት ለመሸጥ ያወጡት ማስታወቂያ ይህ ይመስላል።ዝርዝሩን በማስታወቂያ ያገኙ!!
21/01/2026

የጨረታ ማስታወቂያ

የይ/ዓለም ከተማ ጤና ጣቢያ የተለያየ የአሮጌ/ ያገለገሉ ንብረት ለመሸጥ ያወጡት ማስታወቂያ ይህ ይመስላል።

ዝርዝሩን በማስታወቂያ ያገኙ!!

አስደሳች ዜናየማርበርግ ቫይረስ በሽታ በሀገራችን መከሰቱን አስከትሎ ወረርሽኙን በአጭር ጊዜ ለመከላከል እና ለመቆጣጠር እንዲሁም የህብረተሰባችንን ጤና ለመጠበቅ የጤና ሚኒስቴር፣ ከኢትዮጵያ የ...
04/12/2025

አስደሳች ዜና

የማርበርግ ቫይረስ በሽታ በሀገራችን መከሰቱን አስከትሎ ወረርሽኙን በአጭር ጊዜ ለመከላከል እና ለመቆጣጠር እንዲሁም የህብረተሰባችንን ጤና ለመጠበቅ የጤና ሚኒስቴር፣ ከኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ፣ከክልል ጤና ቢሮዎች እና ከሁሉም ባለድርሻ አካላት ጋር በጋራ በመሆን በሽታዉን የመከላከል እና የመቆጣጠር ስራዎች ተጠናክሮ የቀጠለ ሲሆን፤
በዛሬው ዕለት ከአሜሪካ መንግስት በተደረገ ድጋፍ ለበሽታው ተጋላጭነት ላላቸው የማህበረሰባችን ክፍሎች በሽታውን ለመከላከል የሚያግዝ “Sabin single-dose cAd3 Marburg vaccine” የተባለ የማርበርግ ክትባት ተረክበናል።

ይህ የማርበርግ ክትባት በተለያዩ የማርበርግ በሽታ ወረርሽኝ የተከሰተባቸው ሀገራት በሽታውን ለመከላከል እና ለመቆጣጠር ዕገዛ እንዳደረገ የተገለፀ ሲሆን ይሄን ተሞክሮ በመውሰድ ተጋላጭነታቸው ከፍተኛ ለሆኑ ባለሙያዎቻችን እና የህብረተሰባችን ክፍሎች ለማቅረብ ዝግጅቶችን ጨርሰናል።

03/12/2025
አሳሳቢ የኤች አይ ቪ/ኤድስ ስርጭትአዲስ አበባ ከአገር አቀፉ ምጣኔ በከፍተኛ ሁኔታ ከፍ ብሏል! በኢትዮጵያ የኤች አይ ቪ ቫይረስ ስርጭት አዲስ መረጃዎች ወጥተዋል። የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤ...
03/12/2025

አሳሳቢ የኤች አይ ቪ/ኤድስ ስርጭት
አዲስ አበባ ከአገር አቀፉ ምጣኔ በከፍተኛ ሁኔታ ከፍ ብሏል!

በኢትዮጵያ የኤች አይ ቪ ቫይረስ ስርጭት አዲስ መረጃዎች ወጥተዋል። የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ባካሄደው የቅርብ ጊዜ ጥናት መሠረት፣ በአዲስ አበባ ከተማ የተመዘገበው የስርጭት ምጣኔ ከአገር አቀፉ አማካይ በከፍተኛ ደረጃ ከፍ ብሎ ተገኝቷል።

ቁልፍ ግኝቶች

* የአዲስ አበባ የስርጭት ምጣኔ: 3.14 %
* የሀገር አቀፍ የስርጭት ምጣኔ: 0.83%

ይህ ማለት በአዲስ አበባ ያለው የስርጭት መጠን ከሀገሪቱ አማካይ በእጅጉ ከፍ ያለ መሆኑን ያመለክታል።
በቫይረሱ የተጠቁ ሰዎች ቁጥር እና ዕድሜ ስርጭት

በኢትዮጵያ የኤች አይ ቪ ቫይረስ ጋር የሚኖሩ ሰዎች: ከ600 ሺሕ በላይ ናቸው።

* በዕድሜ ክልል የተያዙ ሰዎች ድርሻ:

* ከ0 እስከ 14 ዓመት (ሕፃናት): 16%

* ከ15 እስከ 24 ዓመት (ወጣቶች): 34%

* 25 ዓመት እና ከዛ በላይ (አዋቂዎች): 51%

የ2024/2025 የዓመት ግምቶች እና ሞት 😔

* በ2024/2025 በጀት ዓመት አዲስ በኤች አይ ቪ ይያዛሉ ተብለው የተገመቱ ዜጎች: 7,962።

* በየዓመቱ በአማካይ በኤች አይ ቪ/ኤድስ ምክንያት ሕይወታቸውን የሚያጡ ሰዎች: 9,560።

በሀገር አቀፍ ደረጃ ከኤች አይ ቪ/ኤድስ ጋር እንደሚኖሩ ከሚገመተው ሰዎች መካከል ራሳቸውን አውቀው መድኃኒት የጀመሩት: 94%

Via VOA Amharic

የይርጋለም ከተማ መጀመሪያ ደረጃ ጤና ክብካቤ አሃድ ልዩ ተሸላሚ ሆኗል።የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ጤና ቢሮ የ2017 በጀት ዓመት አፈጻጸም የገመገመ ስሆን ይርጋለም ከተማ መጀመሪያ ደረ...
20/10/2025

የይርጋለም ከተማ መጀመሪያ ደረጃ ጤና ክብካቤ አሃድ ልዩ ተሸላሚ ሆኗል።

የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ጤና ቢሮ የ2017 በጀት ዓመት አፈጻጸም የገመገመ ስሆን ይርጋለም ከተማ መጀመሪያ ደረጀ ጤና ክብካቤ በክልል ውስጥ ካሉ ጤና ተቋማ የተሻለ አፈጻጸም በማስመዝገብ አንድ ኮንፒዩተር ፣ የ400,000 ሺህ ብር መድሃኒት፤ መዳሊያ፣ እና ሰርተፍኬት ተሸልሟል ።

እንኳን ደስ አላችሁ!? እንኳን ደስ አለን🙏

ጥቅምት 10/2018 ዓ/ም

የሲዳማ ክልል ጤና ብሮ መግለጫ በሲዳማ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት የማህበረሰብ አቀፍ የጤና መድህን ተጠቃሚዎች ቁጥር እየጨመረ መጥቷል፦ ዶ/ር ሰላማዊት መንገሻ በክልሉ የማህበረሰብ አቀፍ የጤና...
18/10/2025

የሲዳማ ክልል ጤና ብሮ መግለጫ

በሲዳማ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት የማህበረሰብ አቀፍ የጤና መድህን ተጠቃሚዎች ቁጥር እየጨመረ መጥቷል፦ ዶ/ር ሰላማዊት መንገሻ

በክልሉ የማህበረሰብ አቀፍ የጤና መድህን ተጠቃሚዎች ቁጥር እየጨመረ መምጣቱን የሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ ሀላፊ ዶ/ር ሰላማዊት መንገሻ ጉዳዩን አስመልከቶ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ተናግረዋል፡፡

መግለጫውን የሰጡት የሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ ሀላፊ ዶ/ር ሰላማዊት መንገሻ የማህበረሰብ አቀፍ የጤና መድህን አገልግሎት ዜጎች አስቀድመው በሚከፍሉት አነስተኛ መዋጮ ያልተገባ የጤና ወጪ ውስጥ እንዳይገቡ የሚያደርግ መሆኑን አብራርተው በዘርፉም በርካታ ለውጦች መመዝገባቸውን ጠቁመዋል።

በክልሉ ባለፉት አምስት ዓመታት በማህበረሰብ አቀፍ የጤና መድህን አገልግሎት የተከናወኑት ስራዎች አበረታች መሆናቸውን በማውሳት፤ ከአገልግሎት አሰጣጥ ጋር ተያይዞ ከመድሃኒት አቅርቦት ጋር የሚታዩ ችግሮችን ለመፍታት ከአምስት ዓመት በፊት 1ብቻ ከነበረበት በአሁኑ ወቅት ወደ 26 የማህበረሰብ መድሃኒት ቤቶችን በመክፈት ለአገልግሎት ማብቃት መቻሉን ሀላፊዋ ገልፀዋል።

በክልሉ በ2017 በጀት ዓመት በማህበረሰብ አቀፍ የጤና መድህን አገልግሎት ከ413ሺህ በላይ አባወራዎች በዚህም 2 ሚሊዮን ዜጎችን ተጠቃሚ መሆናቸውን በመጥቀስ፤ የማህበረሰብ አቀፍ የጤና መድህን ፍትሃዊና ጥራቱን የጠበቀ የጤና አገልግሎት ከመስጠትና የመደጋገፍና የመተጋገዝ ዕድሎችን እያሰፋ ያለ መሆኑን አስረድተዋል።

የቢሮ ኃላፊዋ አያይዘውም በተያዘው በጀት አመትም 680 ሺህ አባወራዎችን በዚህም 3.4 ሚሊዮን ዜጎችን በማህበረሰብ አቀፍ የጤና መድኅን መርሃ-ግብር ተጠቃሚ እንዲሆኑ ለማድረግ ግብ ተጥሎ የዕቅድ አካል በማድረግ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡

የነባር አባላት እድሳት እና የአዲስ አባላት ምዝገባ ከጥቅምት 1/2018 ዓ.ም እስከ ህዳር 30/2018 ዓ.ም ድረስ እንደሚያካሂድ በመግለጫው ጠቁመዋል፡፡

የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን መርህ መደጋገፍ ስለሆነ አባላት ቢታመሙም ባይታመሙም ህመም መቼ እንደሚገጥም ስለማይታወቅ አባልነታቸውን በወቅቱ ማደስ እንደሚኖርባቸው እና ህብረተሰቡ ራሱንና ቤተሰቡን ካልታሰበ የድንገተኛ ወጪ ለመጠበቅ ይገባዋል በማለት አጠቃላይ በገቢ እርከን ደረጃ በክልሉ ባሉ የከተማ አካባቢዎች ከፍተኛ 1ሺህ930 ብር ፣መካከለኛ 1ሺህ 310 ብር ዝቅተኛ 1000 ብር እንዲሁም በገጠር መካከለኛ 1,260 ከፍተኛ 1,710 እና ዝቅተኛው 1000 መሆኑን ገፀዋል፡፡

ተግባራትን በጋራ በመፈፀም ቁልፍ መሆኑን በማውሳት በ2018 ዓ.ም ለሚከናወነው ስራም በቅንጅት እንዲሰራ ጥሪ አስተላልፈዋል።

የሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ

HIV ቫይረስ በደም ውስጥ ከገባ ከ1 እስከ 2 ወር በሆነ ጊዜ ውስጥ የሚታዩ ምልክቶች የኤች አይ ቪ ኤድስ ቫይረስ ምልክቶች አንዳንድ ጊዜ ለረጅም ጊዜ ሊደበቁ ይችላሉ።ይሁን እንጂ ቫይረሱ ወ...
15/10/2025

HIV ቫይረስ በደም ውስጥ ከገባ ከ1 እስከ 2 ወር በሆነ ጊዜ ውስጥ የሚታዩ ምልክቶች

የኤች አይ ቪ ኤድስ ቫይረስ ምልክቶች አንዳንድ ጊዜ ለረጅም ጊዜ ሊደበቁ ይችላሉ።

ይሁን እንጂ ቫይረሱ ወደ ሰውነታችን ከገባ ከ1 እስከ 2 ወራት ባሉት ጊዜያት ውስጥ 50 በመቶ የኤች አይ ቪ ኤድስ ተጠቂዎች በቅድሚያ የሚገጥማቸው የህመም ምልክቶች (አኪዩት ሪትሮቫይራል ሲንዱረም) አሉ።

እነዚህ የህመም ምልክቶችን ካስተዋልን ታዲያ ኤች አይ ቪ ፖዘቲቭ ልንሆን ስለምንችል ወደ ህክምና ተቋማት ማምራት ተገቢ ነው ይላሉ የህክምና ባለሙያዎች።

ኤ አር ሲ (አኪዩት ሪትሮቫይራል ሲንዱረም) ሰውነታችን የተለያዩ ባክቴሪያዎችን እና ቫይረሶችን ለመቋቋም የሚያስችለውን አንቲቦዲስ ከማምረቱ በፊት የሚከሰቱ የመጀመሪያ የህመም ስሜቶች ናቸው።

ኤች አይ ቪ ልቅ በሆነ የግብረ ሰጋ ግንኙነት፣ የደም ንክኪ፣ ስለታማ ነገሮችን በመጋራት እንዲሁም በእርግዝና ወቅት ከእናት ወደ ልጅ እንደሚተላለፍ ይታወቃል።

እርግጥ ነው በርካቶቻችን ስለ ኤች አይ ቪ ኤድስ ያለን ግንዛቤ አነስተኛ ነው የሚባል ባይሆንም ከዚህ በታች የዘረዘሩት ግን ምናልባትም የሌላ ህመም ምልክቶች ናቸው በሚል ቸል እያልናቸው ለሞት ሊዳርጉን ስለሚችሉ ብናስተውላቸው መልካም ነው።

1. ትኩሳት

ትኩሳት የመጀመሪያው የኤ አር ሲ ምልክት ሲሆን፥ ከጉሮሮ ህመም፣ ከሊምፍ (በደም ውስጥ የሚገኝ ፈሳሽ ንጥረ ነገር) አመላላሽ ቱቦዎች እብጠት እና ከድካም ጋር ይያያዛል።

2. ከፍተኛ የድካም ስሜት

ሰውነታችን በኢንፌክሽን (ማመርቀዝ) ሲዳከም የመቆጣት ምላሽ ይሰጣል። ይህም ለህመሞች የሚሰጠው ምላሽ ከፍተኛ የድካም ስሜት እንዲሰማን ያደርጋል።

ይህም የኤች አይ ቪ ኤድስ ምልክት ሊሆን ይችላል ተብሏል።

3. የመገጣጠሚያ አጥንቶች ህመም

4. የጉሮሮ ህመም እና ከፍተኛ የራስ ምታት

5. የቆዳ መንደብደብ

6. ማቅለሽለሽ፣ ማስመለስ እና ተቅማጥ

ከ30 እስከ 60 በመቶ በቫይረሱ የተጠቁ ሰዎች ለአጭር ጊዜ የሚቆይ የተቅማጥ በሽታ ያጋጥማቸዋል።

7. ክብደት መቀነስ

8. ደረቅ ሳል

ለሳምንታት የዘለቀ ደረቅ ሳልም በቫይረሱ መያዝን ሊያመላክት ይችላል።

9. የሳንባ ኢንፌክሽን

10. የሌሊት ላብ

ግማሽ የሚሆኑት የኤች አይ ቪ ኤድስ ተጠቂዎች በሌሊት ላብ ይጠቃሉ። ይህም ከመኝታ ክፍሎች ሙቀት ጋር የተያያዘ አለመሆኑን ጥናቶች ያሳያሉ።

11. የጥፍር ቀለም እና ቅርፅ መቀየር

የጥፍሮች መታጠፍ እና መጥቆር ቫይረሱ ወደ ሰውነታችን እንደገባ ሊታዩ ይችላሉ።

12. የመተንፈሻ እና የመራቢያ አካላት ህመም

13. መንቀጥቀጥ እና የእግር እና እጅ ጡንቻዎች መልፈስፈስ

የእጅ እና እግር ጡንቻዎች አቅማ ማጣት ወይም መንቀጥቀጥ ለኤች አይ ቪ ኤድስ ቫይረስ ብቻም ሳይሆን ለስኳር በሽታ መጋለጥንም ሊያሳይ ይችላል።
14. የወር አበባ ኡደት መዛባት።

Heppataytesete Xisso  *****************************Hawaasa, Birra 05, 2018 (SBC)🎯 Heppataytesi  Vayrese noonsa manni bis...
15/10/2025

Heppataytesete Xisso

*****************************
Hawaasa, Birra 05, 2018 (SBC)

🎯 Heppataytesi Vayrese noonsa manni bisu kikkisamme agadha hasiissanno.

🎯 Heppataytesi Vayrese hanqafamatenni, cu’mamatenni woy sagale mitteenni itatenni disa’’anno.

🎯 Mittu manchinni woleho sa’annohu mundeete kikkisammenni woy daafantino sagalenna wayinni ubbara dandiitanno.

🎯 Heppataytesi B woy C Xisso mitte higge ubburo duucha higge malaatta leellishshanno.

🎯 Lowo manni Heppataytesi B woy C Xissonni amadamiro dirrate mereero malaatta leeltukkinni keeshsh*tara dandiitanno. Tenne yannara infekishiine suutunni kurkurte afale hawartara dandiitanno. Konnira xisso leeltinonsa manni xaaddotenni fayyimmate uurrinshara hasiissanno xagishshu owaante adha hasiissanno.

🎯 Heppataytesi B woy C Xisso wo’munku buhira noo qansoota amaddara dandiitanno.
Marqu qaaqquulli tini xisso amaddino amawiinni adhe ilamara dandaanno. Qolteno qaaqquullu taaltino sagale hoongenni woy qarqaru keeraanchimma daafammenni tenne xissonni amadamara dandaanno.

🎯 Baalante Heppataytesite Xissora kittiwaatu noose.
Kayinnilla Heppataytesi C nna D woy E xissora kittiwaatu dino. Togoo dani Heppataytesera marfe horoonsi’ratenni buuxishsha assatenninna qarqaru keeraanchimma agadha gargadhate dooggate.

🎯 Wo’manti tenne xisso infekshiine jawu garinni afale tayissanno dikkitino. Roorinni Heppataytesi A nna mudditannoti heppataytese B wo’munni wo’ma hurate kaayyonsa gamu mannira lowote.

🎯 Hasiissanno xagishsha adhatenninna heeshshote gade ikkito qorophote amadatenni xisso murrisira dandiinanni.

👉 Heppaataytes gargadha, xagisi’ranna hedeweelcho tunconni gata dandiinanni xisso ikkitinota hegersa hasiissanno.

Address

Sidama Yirgalem
Yirgalem

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Yirgalem Primary Health Care Unit posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share