21/04/2020
# መጽሐፍ ቅዱስ ፍጹም የእግዚአብሔር ቃል ነው!!!
መጽሐፍ ቅዱስ የእግዚአብሔር ቃል መሆኑን የሚደግፉ ሁለት ዓይነት ማርጋገጫዎች አሉ::
1). ውስጣዊ ማረጋገጫ እና
2). ውጫዊ ማረጋገጫ ናቸው::
1). ውስጣዊ ማረጋገጫ :- የምንለው በመጸሐፍ ቅዱስ በራሱ ውስጥ የተመለከቱት እወነታዎች እና መጽሐፋ በራሱ የሚሰጣቸው ምስክርነቶች ናቸው::
:- መጽሐፍ ቅዱስ ራሱ የእግዚአብሔር ቃል መሆኑን በብዙ መቶ በሚቆጠሩ የንባብ ክፍሎቹ ያርጋግጣል:: ለምሳሌ ያህል :- ዘፍ 1:1- እና 2 :1- እግዚአብሔርም ...አለ
ዘዳ 6:6-9 እኔ ዛሬ አንተን የማዝዘውን ይህን ቃል
ኢያ 1:8 የዚህ ሕግ መጽሐፍ ... ብዬ አላዘዝሁምን?
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ እግዚአብሔርም አለ እግዚአብሔርም እንዲህ ይላል የሚሉ ቃላት እጅግ በጣም በመደጋገም ተጽፈዋል:: ይህም የተናጋሪው ቃል ከራሱ አፍ በቀጥታ መውጣቱን ያሳያል:: ሌሎችም ጥቅሶች የመጽሐፍ ቅዱስን የእግዚአብሔር ቃልነት ያርጋግጣሉ::
2ሳሙ 22:31 መዝ 1:2 12:6 ምሳ 30:5-6 ኢሳ 55:10 ኤር 15:16 ዳን 10:21 ዘው 22:38 ዘዳ 18:18-20 ኤር 1:9 23:16-22 ሕዝ 2:7
:- ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ከብሉይ ኪዳን መጽሐፍት በመጥቀስ የእግዚአብሔር ቃልነቱን አረጋግጧል::
በብሉይ ኪዳን ውስጥ የተፃፋትን ታሪኮች ተአምራቶች በመጥቀስ እውነተኛነታቸውን አረጋግጧል::
ለምሳሌ:-
- የፍጥረት ታሪክ በዘፍጥረት እንደተፃፈው መሆኑን ማቴ 19:4
- የአዳም እና የሔዋን ታሪክ እውነተኛነቱን ማቴ 19:4-6
- ሰለ አቤል ማቴ 23:35
- ሰለ ሰይጣን ሉቃ 11:18 ሕዝ 28:11-19
- ሰለ ኖህ ማቴ 24:37-38
- ሰለ ዮናስ ማቴ 12:39
- ሰለ ሎጥ ሚስት ሉቃ 17:32 ብዙ ማለት ይቻላል.......
ኢየሱስ ክርስቶስ የብሉ ኪዳን መጽሐፍትን በመጥቀሱ እና በርሱም ላይ የሚፈጸሙ ትንቢታዊ ቃሎችን ጠቅሶ እውነተኛነቱን በማረጋገጡ የመጽሐፍቱን የእግዚአብሔር ቃልነት ይበልጥ አሳይቷል::
:- ቀጥተኛ የሆነ የእግዚአብሔር ቃል በፀሐፊዎቹ ነብያት በኩል ተላልፏል::
እግዚአብሔር በተደጋጋሚ በነብያት አፍ ውስጥ በማለፍ ተናግሯል:: እንዲሁም ራሱ በመንፈስ ቅዱስ አማካኝነት እየነዳቸው ቃሉን ሳይጨምሩ ሳይቀንሱ ጽፈዋል::
ለምሳሌ:- 1ነገ 14:18 16:12(34) 2ነገ 9:36 14:25 ዘካ7:7(12) ኤር 37:2 በዚህም ምክኒያት የነብያቱን ቃል የማያከብር የእርሱን ቃል እንዳላከበር ተጽፏል::
1ሳሙ 10:8 13:13-14 15:3 (19,23) ዘዳ 18:19 1ነገ 20:35-36 ብዙ ማለት ይቻላል.......
1ቆሮ 11:23 14:37 7:12 ( ሐዋሪያው ጳውሎስ የራሱን ቃል ከጌታ ቃል ለይቶ አስቀምጧል)
ከዚህ በተጨማሪ መጽሐፍ ቅዱስ ስዎች በራሳቸው ለስዎች የፃፉት ሳይሆን በእግዚአብሔር መንፈስ በመነዳት ቅዱሳን ስዎች የፃፋት እንደሆነ ይናገራል:: 2ጴጥ 1:20-21
2). ውጫዊ ማርጋገጫዎች :- መጽሐፍ ቅዱስ የእግዚአብሔር ቃል መሆኑን በራሱ ብቻ የሚያስረግጥ ሳይሆን ተጠራጣሪዎችን እንኳን ለማሳመን በሚችሉ ብዙ መረጃዎች የተሞላ ነው::
:- የመጽሐፍ ቅዱስ ተከታታይ እና ወጥነቱ
- መጽሐፍ ቅዱስ ተጽፎ ለማለቅ የፈጀው ግዜ ወደ 1600 ዓመታት ያህል ነው:: እንግዲህ በዘፍጥረት ፀሐፊ እና በራዕይ መጽሐፍ ፀሐፊ መካከል ያለው ትልቅ የዘመን እርቀት አለ:: እንዲሁም አምላክ ቃሉን ለማፃፍ የተጠቀመባቸው ሰዎች የተለያየ የእውቅት የአኗኗር የስፍራ ልዩነት ያላቸው ሲሆኑ ታድያ በተለያያየ ዘመናት ላይ የነበሩ የማይተዋውቁ ሰዎች እንዴት ተከታታይነት ያለውን ውጥነት ያለው መጽሐፍት ሊፅፉ ቻሉ? ይህ ማንም ሊከራከርው ያልቻለውእና የተፃፈው በአንድ መንፈስ መሪነት ብቻ መሆኑን ያረጋገጠ እውነት ነው::
:- የመጽሐፍ ቅዱሳዊ መገለጥ ጥልቀት
- መጽሐፍ ቅዱስ እውነትን በሙላት እና በረቂቅነት የሚያሳየንን ያህል የሚያሳይ ሌላ መጽሐፍ በዓለም ላይ የለም:: ፀሐፊዎቹ ሰለዘመናዊ ግኝቶች ምንም እውቀት ሳይኖራቸው የፃፏቸው ነገሮች ዛሬ በሳይነሳዊ ምርምሮች በከርስ ምድር ቁፋሮዎች የበለጠ ሊረጋገጡ ችለዋል:: የእግዚአብሔርን ቃል ረቂቅ ስራዎች እቅድ እና ዓላማን በመግለጥ እንዲሁም ትንቢታዊ ቃቹ ሲፈፀሙ በማየት የእግዚአብሔር ቃልነቱን በቀላሉ ማረጋገጥ ይቻላል:: የምድርንም ክብነት የዝናብን ዑደት የምድርን በሕዋ ላይ መንሳፈፍ የድብ ኮከብ የተፈጥሮን ቅደመ ተከተል ምድር ቅርጸ አልባ እንደነበርች በውኃ የተሸፈነች እንደነበር ተክሎች የሕይውት ጅማሬ መሆናቸውን ሌሎች የተፈጥሮ ጥበቦች ብዙ ማለት ይቻላል....... ገና ከጅማሬው በጥንቱ ዘመን የተፃፈ ሲሆን ዛሬ እንደብርቅ ግኝት በሳይንሱ አለም ተረጋግጠዋል ይህ ድንቅ ነው::
:- በሰነ ፅሁፍ ይዘቱ
-በዚህ ርገድ ሲታይ በእርግጥ በስዎች በራሳቸው ችሎታ አለመፃፋን በፍጥነት ማወቅ ይቻላል:: በውስጡ የሚገኘው ይዘት ሁሉንም የሰነ ፅሁፍ ዘርፎች ያካተተ ነው:: የታሪክ ዘገባዎች ትንቢቶች ቅኔዎች ተውኔቶች የጦርነት የፍቅር ታሪኮች የያዘ ነው:: ይህም በየትኛውም የእውቅት ደርጃ ላይ ያሉ ሰዎችን የመማረክ ኃይል እንዲኖርው አድርጎታል::
:- የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት ታላቅነት
መጽሐፍ ቅዱስ ከሰው እውቀት በላይና ውጪ የሆኑትን ሚስጥር ይገልጣል:: በማንኛውም ጉዳይ ላይ የሚሰጠው ትምህርታዊ ገላለጣ እጅግ በጣም ፍፁም እና ትክክል ሲሆን ጊዜ የማይለውጠው ቴክኖሎጂ የማይሽረውን እውቀት ይገልጣል:: ከዚህም የተነሳ ጥንታዊ መጽሐፍ ውይም ዘመናዊ መጽሐፍ ነው ለማለት ሰለሚይስቸግር ዘላለማዊ ቃል ሊባል ችሏል::
:- የመጽሐፍ ቅዱሱ የማያዳላው ሥልጣን
መጽሐፍ ቅዱስ በማንኛውም የሰው ልጅ ላይ በስልጣን ይናገራል:: የሰውን ሁሉ ሐጢያተኝነት ደካማነት በግልጽ አጋልጧል:: በስዎች ብዕር ቢፃፍም ከስዎች ወደ ስዎች ሳይሆን ከእግዚአብሔር ወደ ሰው የሆነ የስልጣን ቃል ያስተላልፋል:: በነገስታት ላይ በድሆች ላይ በባለጠጎች በመላዕክት ላይ በልዩ ፍጥረት ላይ የፍርድን ቃል የማሳለፍ ስልጣን አለው::
:- የመጽሐፍ ቅዱስ ሉአላዊ ባህሪያት
- የተፃፈ ቃል የሆነው መጽሐፍ ቅዱስ እና ሕያው ስጋ የሆነው ቃል ኢየሱስ ክርስቶስ በተመሳሳይ መልኩ ስልጣናቸው ተግልጧል:: ይህም ማለት ስጋ የሆነው ቃል በጹሑፍ የሰፈርውን ቃል መለኮታዊ ቃል እንደሆነና በመንፈሳዊ ነገሮች ሁሉ ላይ የመበየን ስልጣን እንዲሁም ማንም ሊቃወመው የማይችለው ሉዓላዊነት እንዳለው አመልክቷል::
:- የመጽሐፍ ቅዱስ የመለውጥ ሐይል እና የሕትመት ብዛቱ
- በእለማችን የመጽሐፍ ቅዱስን ይህል ለተለያየ ሕዝቦች እና ቋንቋዎች የተተርጎመ መጽሐፍ የለም:: በሕትመትም ብዛት አንፃር ፈጽሞ ከመጽሐፍ ቅዱስ ጋር የሚወዳደር አይገኝም :: ከዚህም በተጨማሪ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ባለው መልዕክት እና ትምህርት ስዎች ስር ነቀል የሆነ የሕይወት እና የዓላማ ለውጥ ማምጣታቸው መጽሐፍ ቅዱስ የእግዚአብሔር መለኮታዊ ቃል ለመሆኑ ማስርጃ ነው:: ከቃሉም የተነሳ የብዙ እልፍ ግለሰቦች እንዲሁም ሀገራት ታሪክ ተለውጧል:: ሰውን የማንፃት የመቀደስ የማጽደቅ እግዚአብሔር ወደ መምሰል የመለውጥ ችሎታው ያለ ጥርጥር የእግዚአብሔር ቃል ለመሆኑ ማስረጃ ነው::
ከሐዋሪያ ይዲድያ ጳውሎስ:- ለእግዚአብሔር የሚሳነው ነገር የለምና!!!