25/02/2026
የመልካምነት ጉዞ፦ የረቂቅ እና የስለ እናት አጋርነት!
የረቂቅ ትምህርትና ስልጠና ኦቲዝም ማዕከል የማኔጅመንት አባላት "ስለ እናት" በጎ አድራጎት ድርጅትን በመጎብኘት ማህበራዊ ኃላፊነታቸውን ተወጥተዋል።
ይህ ጉብኝት ማህበራዊ ግዴታን ከመወጣት ባለፈ፣ በሁለቱ ተቋማት መካከል ለሚደረግ ጠንካራ የጋራ ስራ መሰረት የጣለ ነበር። በዚህም መሰረት፦
ታሪካዊ ስምምነት በረቂቅ ትምህርትና ስልጠና ኦቲዝም ማዕከል ስር የሚንቀሳቀሰው ረቂቅ ዓለም በጎ አድራጎት እና ስለ እናት በጎ አድራጎት ድርጅት በጋራ ለመስራት የሚያስችላቸውን የሁለትዮሽ ስምምነት ለመስራት የተስማሙ ሲሆን በቅርብ ቀን በይፋ እንደሙፈራረ ተወያይተዋል ።
🌟 የስምምነቱ ዓላማ ይህ ትብብር በተለይም በልዩ ፍላጎት ያላቸው ህፃናት ላይ ድጋፍ ለሚፈልጉ ወገኖቻችን እና በኦቲዝም ዙሪያ ለሚሰሩ ስራዎች አዲስ አቅም የሚፈጥር ሲሆን፣ በጋራ በመቆም የተሻለ ለውጥ ለማምጣት ያለመ ነው።
"አብሮነት ለተሻለ ነገ!"