30/05/2026
የአንድ ጤና/one health/ ፕሮግራም ተላላፊ የሆኑ በሽታዎችን ለመከላከል የጎላ ድርሻ እንደአለዉ ተገለፀ ። ከአቡራሃሞ እና ከኡራ ወረዳ ሴክተር መ/ቤቶች ከተወጣጡ የቴክኒክና የስትሪንግ ኮሚቴ ጋር በአንድ ጤና ፕሮግራም አተገባበር ላይ ያተኮረ ዉይይት በአሶሳ ከተማ ተካሄዷል ።
የአንድ ጤና ፕሮግራም የሚመለከታቸው ሴክተር መ/ቤቶችን ባካተተ መልኩ የጋራ የስምምነት ሰነድ በመፈራረም ወደ ሥራ ከገባ አመታትን ከአምስት አመት በላይ እያስቆጠረ ቢሆንም በተፈለገው መልኩ ወደ ሥራ በመግባት ዉጤት እያስመዘገበ አይደለም ።
ይህንን ችግር ለመቅረፍ እና ፕሮግራሙን ወደ ሥራ ለማስገባት የንቅናቄ መድረክ መዘጋጀቱን የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ጤና ቢሮ የህብረተሰብ ጤና አደጋዎች ቁጥጥር እና ምላሽ አሰጣጥ ዳይሬክተር ተወካይ አቶ ሰኚ መኮነን ገልጸዋል ።
የአንድ ጤና ፕሮግራም በሴክተሮች መካከል ያለዉን ቅንጅታዊ አሰራር በማጠናከር ተላላፊ የሆኑ በሽታዎችን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የጎላ ድርሻ ስለአለው የሚመለከታቸው ሴክተሮች ለፕሮግራሙ ትኩረት መስጠት እንደአለባቸዉ አቶ ሰኚ ተናግሯል ።
አቶ ሰኚ አክለውም አሁን በዓለም ላይ ካለዉ የአየር ንብረት ለዉጥ፣የአመጋገብ ሥርዓት መቀየር፣ግሎባላይዜሽን ጋር ተያይዞ የሚከሰቱ የጤና እክሎችን ለመከላከል የአንድ ጤና/one health/ፕሮግራም ተግባራዊ ማድረግ አማራጭ የለለው ተግባር መሆኑን አስረድተዋል ።
በማነቃቀያ መድረኩ ላይ ከአንድ ጤና በተጨማሪ በወቅታዊ የኢቦላ በሽታ ነባራዊ ሁኔታና የቅድመ ጥንቃቄ ሥራዎች ዙሪያ ከኢትዮጵያ የህብረተሰብ ጤና ኢንሰቲትዩት በመጡ ባለሙያዎች የግንዛቤ ማስጨበጥ ሥራም ተሰርቷል
የመድረኩ ተሳታፊዎች በበኩላቸው አንድ ጤና/one health/ፕሮግራም ተግባራዊ ማድረግ ተላላፊ የሆኑ በሽታዎችን ከመከላከል እና ከመቆጣጠር በተጨማሪ በሴክተሮች መካከል ያለዉን ቅንጅታዊ አሰራር ለማጠናከር የጎላ ድርሻ እንዳለው ተናግረው ለተግባራዊነቱ በትኩረት እንደሚሰሩ ገልጸዋል ።
የንቅናቄ መድረኩ የተዘጋጀዉ በወርልድ ቭዥን ኢትዮጵያ አሶሳ ቅርንጫፍ የገንዘብ ድጋፍ ሥሆን ከማነቃቂያ መድረክ በኋላ የቀጣይ ጊዜያት ሥራዉን ለመስራት የጋራ ዕቅድ በማዘጋጀት መድረኩ ተጠናቋል ።