Benishangul Gumuz Health Bureau

Benishangul Gumuz Health Bureau ጤንነቱ የተጠበቀ ዜጋ እናፍራ
(1)

የአንድ ጤና/one health/ ፕሮግራም  ተላላፊ የሆኑ በሽታዎችን ለመከላከል የጎላ ድርሻ እንደአለዉ ተገለፀ ። ከአቡራሃሞ እና ከኡራ ወረዳ ሴክተር መ/ቤቶች ከተወጣጡ  የቴክኒክና የስትሪን...
30/05/2026

የአንድ ጤና/one health/ ፕሮግራም ተላላፊ የሆኑ በሽታዎችን ለመከላከል የጎላ ድርሻ እንደአለዉ ተገለፀ ። ከአቡራሃሞ እና ከኡራ ወረዳ ሴክተር መ/ቤቶች ከተወጣጡ የቴክኒክና የስትሪንግ ኮሚቴ ጋር በአንድ ጤና ፕሮግራም አተገባበር ላይ ያተኮረ ዉይይት በአሶሳ ከተማ ተካሄዷል ።

የአንድ ጤና ፕሮግራም የሚመለከታቸው ሴክተር መ/ቤቶችን ባካተተ መልኩ የጋራ የስምምነት ሰነድ በመፈራረም ወደ ሥራ ከገባ አመታትን ከአምስት አመት በላይ እያስቆጠረ ቢሆንም በተፈለገው መልኩ ወደ ሥራ በመግባት ዉጤት እያስመዘገበ አይደለም ።

ይህንን ችግር ለመቅረፍ እና ፕሮግራሙን ወደ ሥራ ለማስገባት የንቅናቄ መድረክ መዘጋጀቱን የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ጤና ቢሮ የህብረተሰብ ጤና አደጋዎች ቁጥጥር እና ምላሽ አሰጣጥ ዳይሬክተር ተወካይ አቶ ሰኚ መኮነን ገልጸዋል ።

የአንድ ጤና ፕሮግራም በሴክተሮች መካከል ያለዉን ቅንጅታዊ አሰራር በማጠናከር ተላላፊ የሆኑ በሽታዎችን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የጎላ ድርሻ ስለአለው የሚመለከታቸው ሴክተሮች ለፕሮግራሙ ትኩረት መስጠት እንደአለባቸዉ አቶ ሰኚ ተናግሯል ።

አቶ ሰኚ አክለውም አሁን በዓለም ላይ ካለዉ የአየር ንብረት ለዉጥ፣የአመጋገብ ሥርዓት መቀየር፣ግሎባላይዜሽን ጋር ተያይዞ የሚከሰቱ የጤና እክሎችን ለመከላከል የአንድ ጤና/one health/ፕሮግራም ተግባራዊ ማድረግ አማራጭ የለለው ተግባር መሆኑን አስረድተዋል ።

በማነቃቀያ መድረኩ ላይ ከአንድ ጤና በተጨማሪ በወቅታዊ የኢቦላ በሽታ ነባራዊ ሁኔታና የቅድመ ጥንቃቄ ሥራዎች ዙሪያ ከኢትዮጵያ የህብረተሰብ ጤና ኢንሰቲትዩት በመጡ ባለሙያዎች የግንዛቤ ማስጨበጥ ሥራም ተሰርቷል

የመድረኩ ተሳታፊዎች በበኩላቸው አንድ ጤና/one health/ፕሮግራም ተግባራዊ ማድረግ ተላላፊ የሆኑ በሽታዎችን ከመከላከል እና ከመቆጣጠር በተጨማሪ በሴክተሮች መካከል ያለዉን ቅንጅታዊ አሰራር ለማጠናከር የጎላ ድርሻ እንዳለው ተናግረው ለተግባራዊነቱ በትኩረት እንደሚሰሩ ገልጸዋል ።

የንቅናቄ መድረኩ የተዘጋጀዉ በወርልድ ቭዥን ኢትዮጵያ አሶሳ ቅርንጫፍ የገንዘብ ድጋፍ ሥሆን ከማነቃቂያ መድረክ በኋላ የቀጣይ ጊዜያት ሥራዉን ለመስራት የጋራ ዕቅድ በማዘጋጀት መድረኩ ተጠናቋል ።

በዳንጉር ወረዳ የማንቡክ ጤና ጣቢያ የሚሰጠውን የጤና አገልግሎት ለማሻሻል በትኩረት ሊሰራ እንደሚገባ የክልሉ ጤና ቢሮ አስታወቀ። ቢሮው በተለይ በጤና ጣቢያው በሪፈራል ኦዲት ዙርያ እየተሰሩ ...
27/05/2026

በዳንጉር ወረዳ የማንቡክ ጤና ጣቢያ የሚሰጠውን የጤና አገልግሎት ለማሻሻል በትኩረት ሊሰራ እንደሚገባ የክልሉ ጤና ቢሮ አስታወቀ።

ቢሮው በተለይ በጤና ጣቢያው በሪፈራል ኦዲት ዙርያ እየተሰሩ ያሉትን ስራዎች ከኢሉ የሴቶችና ህፃናት የተቀናጀ የልማት ድርጅት ጋር በመተባበር ድጋፋዊ ጉብኝት አድርገዋል።

ድጋፋዊ ጉብኝቱ በክልሉ ጤና ቢሮ በክሊኒካል ዳይሬክተሬት ስር የሚሰራው የጤና አገልግሎት በጤና ኬላ-ጤና ጣቢያ-ሆስፒታሎች ትስስር በማጠናከር ጥራቱን የጠበቀ የጤና አገልግሎት ለመስጠት ያለመ እንደሆነ ተገልጸዋል።

ከጤና ጣቢያዎችም የተነሱ መሰረታዊ ጥያቄዎችን ተቀብሎ የሚመለከተው የባለድረሻ አካላት በችግሮች ዙርያ ተነጋግሮ የመፍትሄ ሀሳቦችን በማስቀመጥ እየተሰራ መሆኑን የክልል ጤና ቢሮ የጤና አገልግሎት ጥራት ማሻሻያ ባለሙያ የሆኑት አቶ ክብሩ ከበደ በድጋፋዊ ጉብኝት ወቅት ተናግረዋል።

የጤና ተቋት የእርስ በእርስ ትስስርን በማጠናከር በዘርፉ ለህብረተሰቡ የሚሰጠውን የጤና አገልግሎት ለማጠናከር የክልል ጤና ቢሮ ከፍተኛ ባለሙያዎች እያደረጉት ያለው ድጋፋዊ ጉብኝት ተጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል።

የክልሉ ጤና ቢሮ!

ርዕሰ መስተዳድር ክቡር አቶ አሻድሊ ሀሰን ለ1447ኛው የዒድ አል-አድሀ (አረፋ) በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል። ርዕሰ መስተዳድሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው እንኳን ለ1...
26/05/2026

ርዕሰ መስተዳድር ክቡር አቶ አሻድሊ ሀሰን ለ1447ኛው የዒድ አል-አድሀ (አረፋ) በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

ርዕሰ መስተዳድሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው እንኳን ለ1447ኛው የዒድ አል-አድሀ (አረፋ) በዓል በሠላም አደረሳችሁ!! በዓሉ የፈጣሪያችንን መልካም ፈቃድ የምንፈፅምበት፤ ደግነትንና አዛኝነትን በተግባር የምንገልጥበት የበረከት በዓል ይሁንልን በማለት መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
ዒድ ሙባረክ!!!

!كل عام وأنتم بخير بمناسبة عيد الأضحى المبارك لعام 1447هـ
نسأل الله أن يكون هذا العيد المبارك مناسبة نحقق فيها إرادة خالقنا الطيبة، ونجسد فيها قيم الخير والرحمة والعطف في واقع حياتنا، وأن يعيده علينا جميعًا
بالبركات والسلام.
عيد مبارك

የኢትዮጵያ ሚድዋይፎች ማህበር በመተከል ዞን የእናቶች እና ህጻናትን ጤና ከማሻሻል ባለፈ የስነ ተዋልዶ ጤና ላይ አበረታች ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን ነዋሪዎች ተናገሩ።(ግልገል በለስ:-ግንቦ...
26/05/2026

የኢትዮጵያ ሚድዋይፎች ማህበር በመተከል ዞን የእናቶች እና ህጻናትን ጤና ከማሻሻል ባለፈ የስነ ተዋልዶ ጤና ላይ አበረታች ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን ነዋሪዎች ተናገሩ።

(ግልገል በለስ:-ግንቦት 18/2018) ማህበሩ በመተከል ዞን በተመረጡ ወረዳዎች የእናቶችና ህጻናት ጤና ከማሻሻል ባለፈ የስነ ተዋልዶ ጤና ዙሪያ ግንዛቤ በማስፋት ረገድ አበረታች ስራዎች መከናወናቸውን ነዋሪዎች ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ሚድዋይፎች ማህበር በፓዊ ወረዳ ከመንደር 7 ቀበሌ ከተወጣጡ የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር በእናቶች ስነ ተዋልዶ ጤና ዙሪያ ውይይት አካሂዷል።

ማህበሩ በወረዳው የእናቶችና ህጻናትን ጤና ከማሻሻል ባለፈ የቤተሰብ ዕቅድ እና የስነ ተዋልዶ ጤና ላይ አበረታች ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን የፓዊ ከተማ ነዋሪዎች ገልጸዋል።

በኢትዮጵያ ሚድዋይፎች ማህበር የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ፕሮጀክት አስተባባሪ አቶ ቀልቤሳ ተሬሳ፤ በዞኑ አራት ወረዳዎች ማለትም ፓዊ፣ ዳንጉርና ወምበራ ወረዳዎች የተመረጡ ጤና ተቋማት ላይ ለእናቶች ምቹ የጤና አገልግሎት እንዲሰጡ አስፈላጊው ድጋፍ እና ክትትል እየተደረገ መሆኑን አመላክተዋል።

ማህበሩ የእናቶችና ህጻናትን ጤና በዘላቂነት ከማሻሻል ባለፈ፣ የቤተሰብ እቅድ እና ጾታን መሰረት አድርገው የሚደርሱ ጥቃቶችን በመከላከል ረገድ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የገለፁት አስተባባሪው ይሄን አጠናክሮ ለማስቀጠል ከባለድርሻ አካላት ጋር በትብብር እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

በመተከል ዞን ጤና መምሪያ የእናቶችና ህጻናት ጤና ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ አብደላ ኢብራሂም፤ መንግስት ጤናው የተጠበቀ ትውልድ ለማፍራት በሚያደረገው ጥረት ውስጥ ማህበሩ እያከናወነ ያለው ሚና ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል።

ማህበሩ የጤና ተቋማት በሙሉ አቅም ወደ ስራ እንዲገቡና የተሟላ የጤና አገልግሎት እንዲሰጡ እያደረገ ያለው ድጋፍ ተጠናክሮ እንዲቀጥል አስፈላጊው ድጋፍና ክትትል እየተደረገ መሆኑን አስተባባሪው አክለው ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ሚድዋይፎች ማህበር የእናቶችና ህጻናትን ጤና ከማሻሻል ባለፈ በዞኑ በተመረጡ ወረዳዎች ተንቀሳቃሽ የህክምና ቡድን በማቋቋም የህክምና አገልግሎት በመስጠት የሙያ ድጋፍ እያደረገ መሆኑ ተገልጿል ሲል የመተከል ዞን ኮሙዩኒኬሽን መምሪያ ዘገባ ያመላክታል።

በክልሉ የበሽታ ዳሰሳና ቅኝት ለማጠናከር  የሁሉም  ባለድርሻ  አካላት ቅንጅታዊ አሰራር ወሳኝ  መሆኑን  የቤኒሻንጉል  ጉሙዝ  ክልል ጤና ቢሮ ገለፀ። የቤኒሻንጉል  ጉሙዝ  ክልል ጤና ቢሮ ...
26/05/2026

በክልሉ የበሽታ ዳሰሳና ቅኝት ለማጠናከር የሁሉም ባለድርሻ አካላት ቅንጅታዊ አሰራር ወሳኝ መሆኑን የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ጤና ቢሮ ገለፀ። የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ጤና ቢሮ የጤና ክላስተር አሁናዊ ሁኔታ ላይ መክሯል ።

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ጤና ቢሮ የህብረተሰብ ጤና አደጋዎች ቁጥጥርና ምላሽ አሰጣጥ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ መብራቱ በጉኖ የተለያዩ ድንበር ተሻጋሪ የሆኑ በሽታዎች እና በክልሉ የሚከሰቱ ወረርሽኞችን ለመከላከል በክልሉ የበሽታ ዳሰሳና ቅኝት ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ገልጸዋል ።

ይህን ሥራ ዉጤታማ ለማድረግ የሁሉም ባለድርሻ አካላት ቅንጅታዊ አሰራር ወሳኝ መሆኑን አቶ መብራቱ ተናግረዋል።

የዉይይቱ ዓላማ የዓለም ጤና ድርጅት (WHO) በግንቦት 09 /2018 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኦፍ ኮንጎ (DRC) እና በዩጋንዳ በቡንዲቡግዮ (Bundibugio) በቫይረስ ዝርያ የሚመጣ የኢቦላ ቫይረስ በሽታ መከሰቱን አስመልክቶ በተሰጠው መግለጫ መሠረት በክልሉ በሽታውን ለመከላከል እንደሀገር ባሉ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎችና እንደክልል መደረግ በሚገባቸው የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች ዙሪያ ለመወያየትና የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ ለማስቀመጥ መሆኑን ዳይሬክተሩ ገልጸዋል ።

የኢቦላ ቫይረስ በሽታ ከፍተኛ የስርጭት እና የሞት ምጣኔ ያለው በሽታ ሲሆን ከሰው ወደ ሰው በንክኪ በቀላሉ, የሚተላለፍ በመሆኑ የቅድመ ጥንቃቄ ሥራዎች ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አቶ መብራቱ አስረድተዋል ።

ምንም እንኳን በሽታው ከተገኘባቸው አገራት ጋር ቀጥተኛ የድንበር ግንኙነት ባይኖረንም በተለያዩ ምክንያት የህዝብ ለህዝብ እንቅስቃሴ በመኖሩ በክልሉ በተለያዩ አቅጣጫዎች የየብስ መግቢያ እና መውጫ ኬላዎች የልየታ እና የቅኝት ስራዎች በማጠናከር፣የጤና ተቋማት ዝግጁ በማድረግ እንዲሁም የላቦራቶሪ አቅምን የማሳደግ እንዲሁም አስፈላጊው የህክምና ግብአት አቅርቦት ላይ የተጠናከረ የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን ለመስራት የዉይይት መድረኩ መዘጋጀቱን አቶ መብራቱ አክለዉ ገልፀዋል።

ይህንን ሥራ አጠናክሮ ለማስቀጠል ደግሞ የሁሉም አካላት ርብርብ አስፈላጊ በመሆኑ በጤናው ዘርፍ ላይ የሚሰሩ ባለድርሻ አካላት በትኩረት መስራት እንደአለባቸዉ ዳይሬክተሩ አሳስበዋል ።

በዉይይቱ ላይ የኢትዮጵያ የህብረተሰብ ኢንሰቲትዩት ባለሙያዎች፣የክልል ጤና ቢሮ የሚመለከታቸው ክፍሎችና በክልሉ በጤና ዘርፍ ላይ የሚሰሩ ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል ።

PUI የተባለው መንግታዊ  ያልሆነ  ግብረሰናይ ድርጅት የክልሉን የጤና ሥርዓት  ለማጠናከር የተከናወኑ ተግባራት አበረታች  መሆናቸው ተገለፀ ።ድርጅቱ  በአሶሳ ዞን በኩርሙክ ወረዳ በሆራዛብ ...
26/05/2026

PUI የተባለው መንግታዊ ያልሆነ ግብረሰናይ ድርጅት የክልሉን የጤና ሥርዓት ለማጠናከር የተከናወኑ ተግባራት አበረታች መሆናቸው ተገለፀ ።ድርጅቱ በአሶሳ ዞን በኩርሙክ ወረዳ በሆራዛብ ጤና ጣቢያ የተከናወኑ ተግባራት ተገምግሟል ።

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መንግስት ጤና ቢሮ የኦፕሬሽን ዘርፍ ምክትል የቢሮ ሀላፊ አቶ አለም ደበሎ በፕሮጀክቱ ማጠቃለያ መድረክ ላይ ተገኝተው እንደአሉት PUI የተባለው መንግታዊ ያልሆነ ግብረሰናይ ድርጅት የክልሉን የጤና ሥርዓት ለማጠናከር በባለፉት 1 አመት በሆራዛብ ጤና ጣቢያ የተከናወኑ ተግባራት አበረታች ዉጤት የተመዘገበበት መሆኑን ነው ።

ፕሮጀክቱ የጤና ጣቢያውን አገልግሎት ለማሻሻል በጤና ተቋማት አጥር
ዕድሳት፣ለተለያዩ አካላት የአቅም ግንባታ ሥራዎች፣የህክምና ቁሳቁስ እና መድሀኒት የማሟላት እና የተበላሹትን የመጠገን እና የጤና ጣቢያውን የቆሻሻ አወጋገድ ሥርዓት የማሻሻል እና በወረዳው በተለያዩ ጊዜት የሚደረጉ የክትባት ሥራዎች ለመደገፍ የተሰሩ ሥራዎች እጅግ የሚደነቁ መሆናቸው ምክትል የቢሮ ሀላፊው ገልጸዋል ።

የእናቶችና ህፃናት ጤና ለማሻሻል በአምቡላንስ ጥገና፣የጤና ተቋማት የቅብብሎሽ ሥርዓት የማጠናከር፣በበሽታው መከላከል እና መቆጣጠር፣በሥርዓት ምግብ ፕሮግራም ዉጤታማ ሥራዎች መሰራታቸውን አቶ አለም ተናግረዋል ።

አቶ አለም አክለውም እነዚህ የተጀመሩ ሥራዎች ቀጣይነት እንዲኖራቸው ከቢሮ፣ጀምሮ እስከታችኛው መዋቅር ድረስ የሚመለከታቸው አካላት ሥራዉን ማስቀጠል እንደአለባቸዉ አሳስበዋል ።

የአሶሳ ዞን ጤና መምሪያ ሀላፊ አቶ ሙሳ አህመድ በበኩላቸው በድርጅቱ የተጀመሩ ሥራዎች ቀጣይነት እንዲኖራቸው ለህብረተሰቡ ቀጣይነት ባለዉ መልኩ አገልግሎት እንዲሰጥ ለማድረግ በዞኑ በኩል አስፈላጊው ሁሉ ድጋፍ እንደሚደረግ ቃል ገብተዋል ።

የፕሮጀክቱ የምዕራብ ሪጅን አስተባባሪ አቶ ኬን ጋለንግ ይህ ፕሮጀክት በጤና ጣቢያ ለስራቸው እና ለተመዘገቡ ዉጤቶች ከቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መንግሥት ጤና ቢሮ ጀምሮ እሰከማህበረሰቡ ለነበረው ድጋፍና ክትትል ያላቸውን ምስጋና አቀርበዉ የተሰሩ ሥራዎች ቀጣይነት እንዲኖረው ድጋፍና ክትትል መደረግ እንዳለበት ጠይቀዋል ።

ይህን ሥራ የተከናወነዉ ከፈረንሳይ ኢምባሲ CDCS በተገኘው 250 ሺህ ዩሮ መሆኑን ከፕሮግራሙ ለማወቅ ተችሏል

26/05/2026

ከጤና ሚኒስቴር የተሠጠ መግለጫ
በአፍሪካ ስለተከሰተው ኢቦላ ቫይረስ በሽታ እና በኢትዮጵያ እየተደረጉ ያሉ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች
ግንቦት 17 ፣ 2018 ዓ.ም

የዓለም ጤና ድርጅት (WHO) በግንቦት 09 ፣ 2018 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኦፍ ኮንጎ (DRC) እና በዩጋንዳ በቡንዲቡግዮ (Bundibugio) ቫይረስ ዝርያ የሚመጣ የኢቦላ ቫይረስ በሽታ መከሰቱን ያሳወቀ ሲሆን እስከ ትላንት ግንቦት 16፣ 2018 ድረስ በእነዚሁ ሀገራት በአጠቃላይ ከ101 በላይ የሚሆኑ በላቦራቶሪ የተረጋገጡ ታማሚዎች እና ከ900 በላይ ንክኪ ያላቸው ተጠርጣሪዎች የህክምና ክትትል ላይ ይገኛሉ።

የኢቦላ ቫይረስ በሽታ ከፍተኛ የስርጭት እና የሞት ምጣኔ ያለው በሽታ ሲሆን ከሰው ወደ ሰው በንክኪ በቀላሉ ይተላለፋል።

እስከዛሬ ድረስ በሃገራችን ኢትዮጵያ ምንም አይነት በኢቦላ ቫይረስ በሽታ የተጠረጠረ ወይም የታመመ ሰው አልተገኘም።

ምንም እንኳን በሽታው ከተገኘባቸው አገራት ጋር ቀጥተኛ የድንበር ግንኙነት ባይኖረንም የበሽታውን አደገኛነት በመገንዘብ የዓለም ጤና ድርጅት (WHO) እና የአፍሪካ በሽታ ቁጥጥርና መከላከል ማዕከል (Africa CDC) የወረርሽኙን መከሰት ይፋ ካደረገበት ጊዜ ጀምሮ የጤና ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር ፦
- በሁሉም አለም አቀፍ የየብስ መግቢያ እና መውጫ ኬላዎች የልየታ እና የቅኝት ስራዎች በማጠናከር ፣
- በአለም አቀፍ አየር ማረፊያዎች የተጠናከረ ክትትል በማድረግ ፣
- የጤና ተቋማት ዝግጁ በማድረግ እንዲሁም የላቦራቶሪ አቅምን በማሳደግ
- እንዲሁም አስፈላጊው የህክምና ግብአት አቅርቦት ላይ የተጠናከረ የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን እያከናወነ ይገኛል።

የክልሉ ጤና ቢሮ ከጤና ሚኒስቴር ጋር በመተባበር የጤናው ዘርፍ የአገልግሎት እና የአስተዳደር ሪፎርም ዙሪያ ለሚመለከታቸው አካላት የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና እየሰጠ ይገኛል። የክልሉ ጤና ቢሮ...
25/05/2026

የክልሉ ጤና ቢሮ ከጤና ሚኒስቴር ጋር በመተባበር የጤናው ዘርፍ የአገልግሎት እና የአስተዳደር ሪፎርም ዙሪያ ለሚመለከታቸው አካላት የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና እየሰጠ ይገኛል።

የክልሉ ጤና ቢሮ የመጀመሪያ ዙር የተሰሩ የሪፎርም ስራዎች ያጠናቀቀ ሲሆን ከጤና ሚኒስቴር ከተሰራው ሪፎርም ጋር የማመሳከር እና የማናበብ ስራም እየተሰራ እንደሚገኝ ይታወቃል።

የክልሉ ጤና ቢሮ ፕሮግራም ዘርፍ ምክትል ቢሮ ሀላፊ አቶ አብዱልሙኒም አልበሸር እንዳሉት አጠቃላይ የጤናው ዘርፍ የፊዴራል ሲቭል ሰርቪስ መነሻ ያደረገ እና ሁሉም የቢሮ ማኔጀሜንት አዉቀዉ ወደ ታችኛው መዋቅር ላይ መስራት እንዳለበት አሳስበዋል።

ሪፎርሙ ዘርፉን ወደ ዲጂታል ለማሸጋገር ትልቅ ፋይዳ እንዳለው ያስታወቁት ሀላፊው በዘርፉ ብቁና ተወዳዳሪ ባለሙያዎችን ለመፍጠር እንደሚረዳም አስታውቋል ።

ከጤና ሚኒስቴር የመጡ እና የጤና ሚኒስቴር ሪፎርም የአገልግሎትና አስተዳደር አማካሪ ዶክተር ተካልኝ ብራሀኔ የጤናዉን ዘርፍ የሪፎርም መነሻዎች፣ ተግዳሮቶችንና መዳረሻዎች እንዲሁም የጤናው ሴክተር ሪፎርም አምዶች በክልል ደረጃ የሚሰሩ ስራዎች ዙሪያ ሰፊ ስልጠና ሰጥተዋል።

በሪፎርሙ ከክልሉ ጤና ቢሮ ጀምሮ ፣አጠቃላይና የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታሎች፣ጤና አጣባበቅ ጣቢያዎች እንዲሁም ጤና ከላዎች ድረስ የሚተገበር ሲሆን ለተግባራዊነቱም ሁሉም ባለድርሻ አካላት የበኩላቸውን ድርሻ እንዲወጡም ጥሪ አቅርበዋል።

በመድረኩ ላይ የጤና ቢሮ ተጠሪ ተቋማት፣ የጤና ቢሮ የማኔጀሜንት አባላትና የጤና ሚኒስቴር የሪፎርም አማካሪዎች ተገኙተዋል።

የክልሉ ጤና ቢሮ!

በክልሉ የኤች አይ ቪ ኤድስ ስርጭትን ለመከላከልና ለመቆጣጠር በጤና ተቋማት የሚደረገውን የጸረ ኤች አይ ቪ ህክምና የክሊኒካል ሜንተርሽፕ ድጋፍና ክትትል ስራ ማጠናከር እንደሚገባ የክልሉ ጤና...
25/05/2026

በክልሉ የኤች አይ ቪ ኤድስ ስርጭትን ለመከላከልና ለመቆጣጠር በጤና ተቋማት የሚደረገውን የጸረ ኤች አይ ቪ ህክምና የክሊኒካል ሜንተርሽፕ ድጋፍና ክትትል ስራ ማጠናከር እንደሚገባ የክልሉ ጤና ቢሮ አስታወቀ።

ቢሮው በጤና ተቋማት የሚደረጉ የኤች አይ ቪ ኤድስ ክሊኒካል ሜንተርሽፕ ድጋፍና ክብካቤ ስራዎችን ለማጠናከር ከዘርፉ ባለሙያዎች ጋር ውይይት አድርጓል።

የክልሉ ጤና ቢሮ የዘርፈ ብዙ ምላሽና ኤች አይ ቪ ኤድስ መከላከልና መቆጣጠር ዳይሬክተር አቶ ታረቀኝ ወዲ በዚህ ወቅት እንዳሉት የኤች አይ ቪ ኤድስ ስርጭትን ለመከላከልና ለመቆጣጠር በጤና ተቋማት የሚደረግ ድጋፍና ክትትል ማጠናከር ይገባል ብለዋል።

የኤች አይ ቪ ኤድስ ህክምናና ምክር አገልግሎት የሚሰጡ ጤና ተቋማት በትኩረት መስራት እንዳለባቸው ያስገነዘቡት አቶ ታረቀኝ በተለይ የዘርፉ ባለሙያዎች በቁርጠኝነት መስራት እንዳለባቸውም አስገንዝበዋል ።

በጤና ቢሮ የዘርፈ ብዙ ምላሽ ኤች አይ ቪ ኤድስ መከላከልና መቆጣጠር ዳይሬክቶሬት የኤች አይ ቪ ክሊኒካል ከፍተኛ ባለሙያ አቶ ይበልጣል ሙለታ በበኩላቸው እንደገለጹት የኤች አይ ቪ ኤድስ የክልኒካል ሜንተርሽፕን ለማጠናከር ጤና ተቋማት እርስ በእርስ ትስስርን ማጠናከር ወሳኝ መሆኑን በመግለፅ ክሊኒካል ሜንተርሺፕ በዘርፉ ለተሰማሩ ባለሞያዎች አቅም ግንባታ ስራ የሚሰራበት መሆኑን በመግለፅ ከክትትልና ግምገማ ስራ በተለየ የምናከናውነው ተግባር በመሆኑ ልዩ ትኩረት በመስጠት መሰራት እንዳለበት ባቀረቡት ሰነድ ላይ ገልፀዋል ።

የአሶሳ አጠቃላይ ሆስፒታል ሚዲካል ዳይሬክተር ዶክተር መብራቱ ወ/መድህን በበኩላቸው ለህብረተሰቡ ጥራት ያለው የህክምና አገልግሎት ለመስጠት ክልኒካል ሜንተርሽፕን ማጠናከር ይገባል ብለዋል።

ስለሆነም ዘርፉን ለማጠናከር በየደረጃው የሚገኙ ባለድርሻ አካላት በባሌቤትነት ስሜት እንዲሰሩም ዶክተር መብራቱ ጥሪ አቅርበዋል።

ለስራው ውጤታማነት በየደረጃው የሚገኙ ጤና ተቋማት የኤች አይ ቪ ኤድስ ምርመራና ህክምና አገልግሎት ማጠናከር እንዳለባቸውም በመድረኩ ላይ ተጠቁመዋል።

በመድረኩ ላይ ዘርፉን ለማጠናከር የሚያስችሉ ሰነዶች በክልሉ ጤና ቢሮ በኩል ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።

የክልሉ ጤና ቢሮ!

Address

Asosa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Benishangul Gumuz Health Bureau posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Benishangul Gumuz Health Bureau:

Share