04/06/2026
የክልሉን የላብራቶሪ ጥራት ለማሻሻያ የዉጫዊ ጥራት ቁጥጥር /EQA / ሥራ ማጠናከር ወሳኝ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መንግስት ጤና ቢሮ ገለፀ። የክልሉ ጤና ቢሮ እና ክልላዊ ላብራቶሪ ከአሶሳ ጤና ጣቢያ ጋር በዉጫዊ የጥራት ቁጥጥር/EQA/ የጋራ ስምምነት ሰነድ ተፈራርሟል ።
የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መንግስት ጤና ቢሮ ምክትል የቢሮ ሀላፊ አቶ አለም ደበሎ
የክልሉን የላብራቶሪ ጥራት ለማሻሻያ የዉጫዊ ጥራት ቁጥጥር /EQA / ሥራ ማጠናከር ወሳኝ መሆኑን ነው ።
በየተቋማቱ የሚሰጠዉን የላብራቶሪ አገልግሎት ጥራት ማሻሻያ ህሙማን ትክክለኛ የሆነ መድሀኒት እንዲያገኙ የሚያደርግ ስለሆነ የዉጫዊ የጥራት ቁጥጥር /EQA/ ሥራ ተጠናክሮ መቀጠል እንደአለበት አቶ አለም ተናግረዋል ።
ቀደም ሲል በሁለቱ አጠቃላይ ሆስፒታሎች ተገድቦ የነበረዉ የዉጫዊ የጥራት ቁጥጥር /EQA/ ሥራ ወደ አሶሳ ጤና ጣቢያ መዉረዱ ማህበረሰቡ ጥራት ያለዉ የጤና አገልግሎት እንዲያገኝ መልካም አጋጣሚ መሆኑን ምክትል የቢሮ ሀላፊው አስገንዝበዋል ።
ምክትል የቢሮ ሀላፊው አክለውም የዉጫዊ የጥራት ቁጥጥር /EQA/ ሥራ ይበልጥ ለማጠናከር የናሙና ቅብብሎሽ ሰንሰለት ማጠናከር ሲቻል በመሆኑ የናሙና ቅብብሎሽ ሰንሰለት ለማጠናከር የጤና ተቋማት በትኩረት መስራት እንደአለባቸዉ አሳስበዋል ።
የመድረኩ ተሳታፊዎች በበኩላቸው የዉጫዊ የጥራት ቁጥጥር /EQA/ ሥራ የጤና ተቋማት በላብራቶሪ አገልግሎት ምን ደረጃ ላይ እንዳሉ ለማወቅና የሚሰጠው የላብራቶሪ አገልግሎት ጥራት ለማስጠበቅ ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል ።
ክልላዊ ላብራቶሪ ቀደም ሲል በወባ፣በቲቢ እና በኤች.አይ.ቨ ኤድስ በሽታዎች በመንግስትና በግል የጤና ተቋማት ላይ የዉጫዊ የጥራት ቁጥጥር /EQA/ ሥራ እንደሚሰራ ከመድረኩ ለማወቅ ተችሏል ።