Alamura Primary Hospital , Hawassa

Alamura Primary Hospital , Hawassa Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Alamura Primary Hospital , Hawassa, Medical and health, Awassa.

የአላሙራ የመ/ደ/ሆስፒታል የብልፅግና ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች የምርጫ የመጨረሻ የድጋፍ ሰልፍ ላይ ተሳተፉ።********************************ዛሬ በቀን 18/09/18 ዓም የ...
26/05/2026

የአላሙራ የመ/ደ/ሆስፒታል የብልፅግና ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች የምርጫ የመጨረሻ የድጋፍ ሰልፍ ላይ ተሳተፉ።
********************************
ዛሬ በቀን 18/09/18 ዓም የአላሙራ የመጀመሪያ ሆስፒታል የብልፅግና ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች በሀዋሳ አለምአቀፍ ስታዲየም በተዘጋጀው የፓርቲው የመጨረሻ የድጋፍ ሰልፍ ላይ ተሳታፊ ሆነዋል።

በአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የነርስ ቀን በደማቅ  ሁኔታ ተከበረ።*********************************በነርሲንግ እና ሚድዋይፈሪ ዳይሬክቶሬት አስተባባሪነት በአላሙራ የ...
24/05/2026

በአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የነርስ ቀን በደማቅ ሁኔታ ተከበረ።
*********************************
በነርሲንግ እና ሚድዋይፈሪ ዳይሬክቶሬት አስተባባሪነት በአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የነርስ ቀን በደማቁ ተከብሯል።

በዕለቱ የተለያዩ የጤና እና የሙያ ነክ ዝግጅቶች የተካሄዱ ሲሆን የነርሲንግ ሙያ በሀገራችን ከጅምሩ አሁን እስከደረሰበት ጊዜ ያለውን የሚዳስስ ገለፃ ፣ግጥሞች፣ ጥያቄና መልስ እንዲሁም የተለያዩ አዝናኝ ፕሮግራሞች ለታዳሚያን ቀርበዋል። በዕውቀት ፣ በክህሎትና በተግባር ምዘና የተሻለ አፈፃፀም ያስመዘገቡ ነርሶችም የማበረታቻ ሰርተፊኬት ተበርክቶላችኋል።

በዕለቱ የሆስፒታሉ ሥራ አስኪያጅ የሆኑት አቶ ዮሴፍ ዮዌ ንግግር ያደረጉ ሲሆን፣ ነርሶች ስለሚያበረክቱት ሙያዊ አስተዋፅኦና በሕክምና አገልግሎት ላይ ያላቸውን ሚና በስፋት ገለፃ አድርገዋል።

አላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል በአራተኛ ሩብ አመት የደም ልገሳ መርሀግብር ለተቋሙ ክብረወሰን የሆነ ከፍተኛ ዩኒት ደም ሰበሰበ፡፡*************************ከቀን 13-14/0...
23/05/2026

አላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል በአራተኛ ሩብ አመት የደም ልገሳ መርሀግብር ለተቋሙ ክብረወሰን የሆነ ከፍተኛ ዩኒት ደም ሰበሰበ፡፡
*************************
ከቀን 13-14/09/18 ዓም ለሁለት ተከታታይ ቀናት በተካሄደ የደም ልገሳ መርሀግብር ለተቋሙ አዲስ ክብረወሰን የሆነ 126 ዩኒት ደም መሰብሰብ ተችሏል። በMCC ኮሚቴ አስተባባሪነት በተካሄደው የበጎ ፈቃደኞች ደም ልገሳ የሆስፒታሉ ማናጅመንት እንዲሁም ሰራተኞች በከፍተኛ ተነሳሽነት በስፋት ተሳትፈዋል።
በዚህ በጎ አድራጎት ተግባር በማስተባበር የተሳተፋችሁ የሆስፒታሉ ማናጅመንት፣ MCC committee እና QIT team እንዲሁም ውድ የሆነውን ስጦታ ላበረከታችሁ የሆስፒታላችን ሰራተኞችና ተገልጋዮች ምስጋና ይገባችኋል።
ደም እንለግስ ህይወትን እንታደግ!

በአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የአስር ወራት አፈፃፀም፣ የ100 ቀናት እቅድና ወራዊ የSBFR አፈፃፀም ሪፖርት ግምገማ ተካሄደ።************************በቀን 04/09/18...
13/05/2026

በአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የአስር ወራት አፈፃፀም፣ የ100 ቀናት እቅድና ወራዊ የSBFR አፈፃፀም ሪፖርት ግምገማ ተካሄደ።
************************
በቀን 04/09/18 ዓም የአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የማናጅመንት አባላት፣ የስራ ክፍል አስተባባሪዎችና የስታፍ አባላት በተገኙበት የአስር ወራት አፈፃፀም፣ የ100 ቀናት እቅድና ወራዊ የSBFR ሪፖርት አፈፃፀም ግምገማ አካሂዷል።
በእለቱም በቀረቡት ሪፖርቶች ዙሪያ እንዲሁም በቀሩ ወራት ውስጥ ትኩረት የሚሰጠባቸው ጉዳዮች ላይ ሰፊ ውይይት የተካሄደ ሲሆን ከተሳታፊዎች ለተነሱት ጥያቄና አስተያየቶች ከመድረክ መልስ ተሰጥቶባቸዋል።

የነፍሰጡር እናቶች ፎረም በአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ተካሄደ።************************ዛሬ በቀን 04/09/18 ዓም በአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የሶስተኛ ሩብ አ...
12/05/2026

የነፍሰጡር እናቶች ፎረም በአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ተካሄደ።
************************
ዛሬ በቀን 04/09/18 ዓም በአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የሶስተኛ ሩብ አመት የነፍሰጡር እናቶች ፎረም ተከናውኗል።
በእለቱም ሁሉም እናቶች ጤናማ የእርግዝና፤ የወሊድና የድህረ-ወሊድ ጊዜ እንዲያሳልፉ አስፈላጊውን የጤና መረጃ እንዲኖራቸው የሚያግዝ የጤና ትምህርት ተሰጥቷል።
በርካታ ነፍሰጡር እናቶች በተሳተፉበት ፎረም ሰፊ ውይይት የተደረገ ሲሆን ከተሳታፊ እናቶችም ለተነሱ ጥያቄዎች ከመድረኩ መልስ ተሰጥቶባቸዋል።

የአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ማናጅመንትና ሰራተኞች ፅዱ ውብና ምቹ የስራ ከባቢን የመፍጠር አካል የሆነውን የፅዳት ዘመቻ በቀን 01/08/18 ዓ.ም በሆስፒታሉ ቅጥር ጊቢ እና በሆስፒታ...
09/05/2026

የአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ማናጅመንትና ሰራተኞች ፅዱ ውብና ምቹ የስራ ከባቢን የመፍጠር አካል የሆነውን የፅዳት ዘመቻ በቀን 01/08/18 ዓ.ም በሆስፒታሉ ቅጥር ጊቢ እና በሆስፒታል ዙሪያ ባሉት መንደሮች ከጠዋት 12:00 ጀምሮ በጋራ አካሂደዋል።

የአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ማናጅመንትና ሰራተኞች "ለሀዋሳ ከፍታ እንሩጥ" በሚል መሪ ቃል በተዘጋጀው የጎዳና ላይ የ5 ኪሎ ሜትር ሩጫ ላይ ተሳታፊ ሆኑ።******************...
26/04/2026

የአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ማናጅመንትና ሰራተኞች "ለሀዋሳ ከፍታ እንሩጥ" በሚል መሪ ቃል በተዘጋጀው የጎዳና ላይ የ5 ኪሎ ሜትር ሩጫ ላይ ተሳታፊ ሆኑ።
************************************
ዛሬ በቀን 18/08/18 ዓም የተዘጋጀውን ሩጫ የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር፣ ኮሜርሺያል ኖሚኒስና አትሌት ገዘሀኝ አበራ በጋራ አዘጋጅተውታል።

የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ አቶ ጥራቱ በየነ፣ የብልፅግና ፓርቲ የሀዋሳ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ማራዶና ዘለቀ፣ አትሌት ገዘሀኝ አበራን ጨምሮ በርካታ የሀዋሳ ከተማ ነዋሪዎችና ሌሎች የክብር እንግዶች ተገኝተዋል።

ዛሬ በቀን 04/08/18 ዓ.ም የአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ማናጅመንትና የስራ አስተባባሪዎች ከተረኛ ባለሙያዎች ጋር በዛሬው እለት የኢየሱስ ክርስቶስ የትንሳኤ መታሰቢያ  የሆነውን የ...
12/04/2026

ዛሬ በቀን 04/08/18 ዓ.ም የአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ማናጅመንትና የስራ አስተባባሪዎች ከተረኛ ባለሙያዎች ጋር በዛሬው እለት የኢየሱስ ክርስቶስ የትንሳኤ መታሰቢያ የሆነውን የፋሲካ በአልን በጋራ አክብረዋል።

ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለኢየሱስ ክርስቶስ የስቅለትና የትንሳኤ በአል በሰላም አደረሰን/አደረሳችሁ!
11/04/2026

ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለኢየሱስ ክርስቶስ የስቅለትና የትንሳኤ በአል በሰላም አደረሰን/አደረሳችሁ!

የአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ማናጅመንትና ሰራተኞች የ 2018 ዓ.ም የ ትንሳኤ በአልን ከአቅመደካሞች ጋር አከበሩ።****************************************በቀን...
11/04/2026

የአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ማናጅመንትና ሰራተኞች የ 2018 ዓ.ም የ ትንሳኤ በአልን ከአቅመደካሞች ጋር አከበሩ።
****************************************
በቀን 03/08/18 የአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ማናጅመንትና ሰራተኞች ከአቅመደካሞች ጋር የትንሳኤ በአልን አክብረዋል።
በ MCC ኮሚቴ አስተባባሪነት ከስታፍ በተሰበሰበ መዋጮ በተዘጋጀው በአል ላይ ከ 50 በላይ ለሚሆኑ በቀበሌያችን የድሀድሀ ተብለው ለተለዩ አቅመደካሞች የዘይትና ዱቄት ድጋፍ ተደርጓል።
በዕለቱም የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት ያስተላለፉት የሆስፒታሉ ስራ አስኪያጅ የሆኑት አቶ ዮሴፍ ዮዌ በዚህ መልካም ተግባር ላይ ከወር ደመወዛቸው መዋጮ በማድረግ ለተሳተፉት የሆስፒታሉ ስታፍ እንዲሁም ዝግጅቱን በማቀናጀት የተሳካ እንዲሆን ላደረጉት ለMCC ኮሚቴ አባላት ምስጋና ያቀረቡ ሲሆን እንዲ ያለው በጎ ተግባር በቀጣይነትም እንደሚካሄድ ቃል ገብተዋል።
በመጨረሻም ድጋፍ የተደረገላቸው አካላት ደስታቸውን በመግለፅ የሆስፒታሉንም ሰራተኞች አመስግነዋል።

የሲዳማ ብሄር የዘመን መለወጫ በዓል የሆነው የፍቼ ጫምባላላ በአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ተከበረ።*****************************************ዛሬ በቀን 07/07/...
16/03/2026

የሲዳማ ብሄር የዘመን መለወጫ በዓል የሆነው የፍቼ ጫምባላላ በአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ተከበረ።
*****************************************
ዛሬ በቀን 07/07/18 ዓም የሲዳማ ብሄር ዘመን መለወጫ የፊቼ ጫምባላላ በዓል በአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ቅጥር ጊቢ ከአካባቢ ማህበረሰብ፣ ከሀገር ሽማግሌ እንዲሁም ከሆስፒታሉ ማናጅመንትና ሰራተኞች ጋር በጋራ በድምቀት ተከብሯል።
በሀገር ሽማግሌዎች ምርቃት በጀመረው ዝግጅት ፣የሲዳማ ብሄር ባህል ፣ ወግ እንዲሁም ትውፊትን የሚያወሱ ዝግጅቶች የተሰናዱ ሲሆን የተለያዩ አዝናኝ ፕሮግራሞችም ለታዳሚያን ቀርበዋል።
በዕለቱ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት ያስተላለፉት የሆስፒታሉ ስራ አስኪያጅ አቶ ዮሴፍ ዮዌ፣ ፍቼ ጫምባላላ የሰላምና የእርቅ በአል መሆኑን አውስተው፣ ያለፈ ቂምና ጥላቻን አስወግደን ወደአዲሱ አመት መሻገር እንደሚገባ በንግግራቸው አፀንኦት ሰጥተዋል።
በመጨረሻም የሲዳማ ብሄር ባህላዊ ምግብ ቀርቦ በጋራ ማዕድ ተቋድሰዋል።

Hawalle Sidaamu Daga Diru sooro Fichee Cambalaallate ayyanira keeruni iillishinke!

እንኳን ለሲዳማ ብሔር የዘመን መለዋጫ ፍቼ ጫምባላላ በዓል በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ !

Address

Awassa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Alamura Primary Hospital , Hawassa posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share