Debark General Hospital

Debark General Hospital This is Debark General Hospital official page

5ኛው ሃገር አቀፍ የጤና መረጃ እና የዲጂታል ጤና ሳምንት መካሄድ ጀመረ5ኛው ሃገር አቀፍ የጤና መረጃ እና የዲጂታል ጤና ሳምንት "በጤና መረጃ እና በዲጂታል ጤና ፈጠራዎች ላይ ዘላቂ ኢንቨስ...
11/05/2026

5ኛው ሃገር አቀፍ የጤና መረጃ እና የዲጂታል ጤና ሳምንት መካሄድ ጀመረ
5ኛው ሃገር አቀፍ የጤና መረጃ እና የዲጂታል ጤና ሳምንት "በጤና መረጃ እና በዲጂታል ጤና ፈጠራዎች ላይ ዘላቂ ኢንቨስትመንት በማድረግ የጤና ትሩፋትን ማፋጠን" በሚል መሪ ቃል መካሄድ ጀምሯል።

መረጃን መሰረት ያደረገ የጤና ስርዓት መገንባት የጤና ስርዓትን የምናሳድግበት ዋነኛው ምሰሶ መሆኑን በመደረኩ የመክፈቻ ንግግራቸው የገለጹት የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ፤ ሁሉን አቀፍ የጤና አገልግሎት ለመስጠት መረጃ መሰረት ነው ብለዋል። ለዚህም የመረጃ ስርዓቱን እስከ ታች ድረስ በመዘርጋት የተቀናጀ እና የተናበበ ስርዓት መዘርጋት መቻሉን አስረድተዋል።

የተቋማት የተገልጋይ መረጃን በአንድ ቋት የማሰባሰብ ስራ እየተሰራ መሆኑን የገለጹት ዶ/ር መቅደስ ዳባ: ለዚህም በበርካታ ተቋማት ከወረቀት ነፃ የኤሌክትሮኒክ ጤና መረጃ (EMR) አሰራር መተግበር መጀመራቸውን ገልጸዋል።
የመረጃ ስርዓቱን በጤና ዘርፍ ለማዘመን ከዩኒቨርሲቲዎች ጋር በመተባበር የጤና መረጃን በካሪኩለም ውስጥ በማካተት ብቁ የሰው ኃይል ለመፍጠር እየተሰራ መሆኑንም አክለዋል።

በጤናው ዘርፍ የተገኙ ውጤቶችን ለማስቀጠል የጤና መረጃ እና ዲጂታል ጤና ፈጠራዎች ላይ ዘላቂ ኢንቨስትመንት ማድረግ አስፈላጊ መሆኑን የተናገሩት በጤና ሚኒስቴር የስትራቴጂክ ጉዳዮች ስራ አስፈጻሚ ዶ/ር ሙሉቀን አርጋው ሲሆኑ: ለአንድ ሳምንት በሚቆየው የጤና መረጃ እና ዲጂታል ጤና ሳምንት ከባለድርሻ አካላት ጋር የተለያዩ ውይይቶች ይደረግብታል ብለዋል።

በመድረኩ በጤናው ዘርፍ የተሻለ የጤና መረጃ አፈጻጸም ላስመዘገቡ ወረዳዎች እና ዩኒቨርሲቲዎች እውቅና ተሰጥቷል።

Ministry of Health,Ethiopia
Dr Mekdes Daba, Minister of Health

''ራስን ለአገልግሎት መስጠት''23ኛውን አመታዊ የኢትዮጵያ ፊዚዮቴራፒ ማህበር ጉባኤ ''ራስን ለአገልግሎት መስጠት'' በሚል መሪ ሃሳብ ተካሄደ።በጤና ሚኒስቴር የሜዲካል አገልግሎትን ወክለው ...
11/05/2026

''ራስን ለአገልግሎት መስጠት''
23ኛውን አመታዊ የኢትዮጵያ ፊዚዮቴራፒ ማህበር ጉባኤ ''ራስን ለአገልግሎት መስጠት'' በሚል መሪ ሃሳብ ተካሄደ።
በጤና ሚኒስቴር የሜዲካል አገልግሎትን ወክለው ንግግር ያደረጉት የስፔሻሊቲና ተኃድሶ ዴስክ ኃላፊ አቶ ኤርሚያስ ሙላቱ እንደገለጹት፣ ጤና ሚኒስቴር ትኩረት ሰጥቶ ከሚሰራባቸው የተሃድሶ አገልግሎቶች መካከል ፊዚዮቴራፒ አንደኛው መሆኑን ጠቅሰው ይህ ዓመታዊ ጉባኤ አዲስ ለሚታቀደው የአምስት ዓመት ስትራቴጂክ እቅድ ዝግጅት የተደራጁ ሃሳቦችን ለመሰብሰብ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው ጠቁመዋል።
ማህበሩ ​የባለሙያዎችን አቅም ለማሳደግና ከአጥንት፣ ከነርቭ እንዲሁም ከጡንቻ ጋር ተያይዘው ለሚመጡ ችግሮች የሚሰጠውን አገልግሎት ለማሻሻል የተቋቋመ ሲሆን፤ በዘርፉ ያሉ ተግዳሮቶችን በመቅረፍ አገልግሎቱን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገርና ከመንግስት ስትራቴጂ ጋር ለማስተሳሰር በቁርጠኝነት እየተሰራ መሆኑን የማህበሩ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ዩሃና ጆቫኒ ገልጸዋል።

Ministry of Health,Ethiopia

ብሔራዊ የመረጃ እና የዲጂታል ጤና ሳምንትNational Data and Digital Health Weekግምቦት 3 እስከ 9 ቀን 2018 ዓ.ምMay 11 - 17, 2026   Ministry of H...
11/05/2026

ብሔራዊ የመረጃ እና የዲጂታል ጤና ሳምንት
National Data and Digital Health Week

ግምቦት 3 እስከ 9 ቀን 2018 ዓ.ም
May 11 - 17, 2026




Ministry of Health,Ethiopia
Dr Mekdes Daba, Minister of Health
Amhara Health Bureau - አብክመ ጤና ቢሮ

ለደባርቅ ጠቅላላ ሆስፒታል ተገልጋዮች በሙሉበሆስፒታላችን ስፔሻሊስት ሐኪሞች ለተወሰኑ ጊዚያት በተለያዩ ምክንያቶች ባለመኖራቸው ምክንያት ታካሚዎች ሲንገላቱ የቆዩ መሆኑ ይታወቃል።አሁን አንድ ...
11/05/2026

ለደባርቅ ጠቅላላ ሆስፒታል ተገልጋዮች በሙሉ
በሆስፒታላችን ስፔሻሊስት ሐኪሞች ለተወሰኑ ጊዚያት በተለያዩ ምክንያቶች ባለመኖራቸው ምክንያት ታካሚዎች ሲንገላቱ የቆዩ መሆኑ ይታወቃል።
አሁን አንድ የውስጥ ደዌ ስፔሻሊስት ሐኪም በጤና ቢሮ በኩል የተመደበልን ሲሆን፣
ደባርቅ ሆስፒታል ከባህርዳር ዩንቨርስቲ ጥበበ ጊዮን ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ጋር በመስማማት አንድ የማህፀንና ፅንስ ስፔሻሊስት ሐኪም ያስመጣ በመሆኑ ሁለቱም ስፔሻሊስት ሐኪሞች ከዛሬ 03/09/18 ዓ.ም ጀምሮ በሆስፒታላችን አገልግሎት መስጠት የጀመሩ በመሆናቸው ቀጠሮ ያላችሁ ታካሚዎች በሙሉ በቀጠሯቹህ ቀን በመምጣት የህክምና አገልግሎቶችን ማግኘት የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን።

ዛሬ የዓለም አቀፍ የእናቶች ቀንን ስናከብር፣ በሕይወታችን ውስጥ በፍቅር፣ በመስዋዕትነት እና በጥንካሬ የማይተካ አሻራ ላኖሩና ለሚያኖሩ እናቶች ሁሉ ክብርና ምስጋና እናቀርባለን።ለልጆቻቸው ህ...
10/05/2026

ዛሬ የዓለም አቀፍ የእናቶች ቀንን ስናከብር፣ በሕይወታችን ውስጥ በፍቅር፣ በመስዋዕትነት እና በጥንካሬ የማይተካ አሻራ ላኖሩና ለሚያኖሩ እናቶች ሁሉ ክብርና ምስጋና እናቀርባለን።

ለልጆቻቸው ህልም ሁሌም የሚተጉ፣ በፍቅር የሚያንጹ እና በተስፋ የሚያቆሙ እናቶች የማህበረሰባችን እውነተኛ ጉልበት ናቸው።

ለሁሉም እናቶች ጤና፣ ፍቅር እና ደስታ እመኛለሁ።

መልካም የእናቶች ቀን!!
Dr Mekdes Daba, Minister of Health

10/05/2026
10/05/2026

የእናቶችና ህጻናት ጤና ለማሻሻል በትኩረት እየተሰራ ነው፡፡

መንግስት የእናቶችና ህፃናት ጤና እንክብካቤን ከመቸውም ጊዜ በላቀ ደረጃ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ይገኛል ።

በመሆኑም የቤተሰብ እቅድ አገልግሎት ማሻሻል ፤ የቅድመ ወሊድና ድህረ ወሊድ ክትትል ማጠናክር፤ እናቶች በሰለጠነ ባለሙያ በህክምና ተቋማት ሂደው እንዲወልዱ ማድርግ፤ የክትባት ሽፋን በከፍተኛ ደረጃ ማሳድግ እንድሁም የህፃናት ህክምና እና የስርአተ ምግብን ማሻሻል ተችሏል ።

በክልላችን የእናቶችና ህጻናት ጤና ለማሻሻል የእናቶች ቀዶ ጥገና አገልግሎት የሚሰጡ ጤና ጣቢያዎችን ቁጥር 40 ማድረስ ተችሏል፤ 924 አንቡላሶችን ተሰራጨተዋል፤ነጻ ህክምና ለእናቶችና ህፃናት ተሰጥቷል ፤ ክትባትና ግብአት ለጤና ተቋማት ማቅረብ ተችሏል ፡፡

በዚህም መሰረት በ2013 ዓ.ም የእናቶች ሞት ምጣኔ ከ100,000 በህይወት ከተወለዱ ህፃናት መካከል 267 የነበረው በ2017/18 ዓ.ም ወደ 141 ማውረድ ተችሏል፤ የህፃናት ሞትን ትርጉም ባለው መልኩ መቀነስ የተቻለ ሲሆን በቀጣይ ዓመታት ከነበረበት 46 ወደ 25 ዝቅ ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ ይገኛል።

የትውልድ ግንባታ ከፅንሰት መጀመር እንዳለበት ይታወቃል፡፡በመሆኑም በመጀመሪያዎቹ 1,000 ቀናት ውስጥ ተገቢ ምግብ ፣ ጤና ፣ እንክብካቤ እና ትምህርታዊ ንቃት ያገኙ ሕፃናት ከፍተኛ የአእምሮ እድገት ፣ የስራ ብቃት እና የማህበራዊ ተሳትፎ እንዲኖራቸው ያደርጋል ፡፡ ይህም በረጅም ጊዜ የሀገር ምርታማነትን ፣ የጤና ወጪ መቀነስን እና የድህነት በር መሰበርን ያመጣል ።

መንግሰት ባለድርሻ አካላትን በማስተባበር በሕፃናት ምግብና ቀዳማይ ልጅነት እድገት ላይ ቀጣይነት ያለው ኢንቨስትመንት በማድረግ ፣ከጤና ፣ ከትምህርት እና ከማህበራዊ ጥበቃ ፖሊሲው ጋር በማቀናጀት እና የሰቆጣ የቃል ኪዳን ስምምነት በመፈራረም በጋራ እያደረገ ያለውን ርብብርብ አጠናክሮ ይቀጥላል፡፡
#አብክመጤናቢሮ


ግንቦት 02/2018 ዓ.ም

የደባርቅ ጠቅላላ ሆስፒታል የ9 ወራት የጤና መድህን አገልግሎት አፈፃፀምን ገመገመ(​ደባርቅ 30/08/2018)የደባርቅ ጠቅላላ ሆስፒታል የማህበረሰብ አቀፍ የጤና መድህን አገልግሎት አሰጣጥን ...
08/05/2026

የደባርቅ ጠቅላላ ሆስፒታል የ9 ወራት የጤና መድህን አገልግሎት አፈፃፀምን ገመገመ

(​ደባርቅ 30/08/2018)

የደባርቅ ጠቅላላ ሆስፒታል የማህበረሰብ አቀፍ የጤና መድህን አገልግሎት አሰጣጥን የተመለከተ የዘጠኝ ወራት የሥራ አፈፃፀም ግምገማ በዛሬው ዕለት አካሄደ። በግምገማው ላይ የሆስፒታሉ ከፍተኛ አመራሮች፣ የክፍል ኃላፊዎችና የሚመለከታቸው ባለሙያዎች ተገኝተዋል።

​በመድረኩ ላይ የዘጠኝ ወራቱን ዝርዝር ሪፖርት ያቀረቡት አቶ ሐዋርያት ማሙዬ እንደገለጹት፣ ሆስፒታሉ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ለማህበረሰብ አቀፍ የጤና መድህን ተጠቃሚዎች ተደራሽነቱን እያሰፋ መቆየቱን በጥቅል መረጃዎች አመልክተዋል።

​እንደ ሪፖርቱ ማብራሪያ፣ ሆስፒታሉ በዘጠኝ ወራት ውስጥ በአጠቃላይ 27,423 ለሚሆኑ የጤና መድህን አባላትና ቤተሰቦቻቸው የሕክምና አገልግሎት የሰጠ ሲሆን፣ ለዚህም በጠቅላላው 14,256,775.44 (አስራ አራት ሚሊዮን ሁለት መቶ ሃምሳ ስድስት ሺህ ሰባት መቶ ሰባ አምስት ከ44/100) ብር ወጪ ተደርጓል።

​የአገልግሎት አሰጣጡን በየሩብ ዓመቱ ሲተነተን የሚከተለውን እንደሚመስል አቶ ሐዋርያት አብራርተዋል

​በመጀመሪያው ሩብ ዓመት፡ 9,367 ታካሚዎች አገልግሎት ያገኙ ሲሆን፣ የገንዘብ መጠኑ 4,845,040.13 ብር ነበር።

​በሁለተኛው ሩብ ዓመት፡ የታካሚዎች ቁጥር መጠነኛ ቅናሽ በማሳየት ወደ 8,398 ዝቅ ቢልም፣ የወጣው ወጪ 4,248,786.11 ብር ሆኖ ተመዝግቧል።

​በሦስተኛው ሩብ ዓመት፡ ከፍተኛው የታካሚ ቁጥር የተመዘገበበት ወቅት ሲሆን፣ 9,658 ታካሚዎች የ5,162,949.20 ብር ዋጋ ያለው ሕክምና አግኝተዋል።

​ይህ አሃዝ እንደሚያሳየው በሦስተኛው ሩብ ዓመት ላይ የታካሚዎች ቁጥርም ሆነ ለአገልግሎቱ የወጣው ወጪ ካለፉት ወራት ጋር ሲነፃፀር ከፍተኛ እድገት አሳይቷል። ይህም የህብረተሰቡ የጤና መድህን አገልግሎት ግንዛቤ ማደጉንና ሆስፒታሉ ያለውን የአገልግሎት አሰጣጥ አቅም እያሳደገ መምጣቱን ያመላክታል።

​ሪፖርቱን መነሻ በማድረግ የሆስፒታሉ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ አለአምላክ ተስፋ እና ሜዲካል ዳይሬክተሩ ዶክተር ፍቃዴ አማረ ከመድረክ ተሳታፊዎች ጋር ሰፊ ውይይት አድርገዋል። በውይይቱም ወቅት የአገልግሎቱን ጥራት ይበልጥ ማሻሻል በሚቻልባቸው መንገዶች፣ በጤና መድህን አጠቃቀምና በሰነድ አያያዝ ዙሪያ የታዩ ጠንካራ ጎኖችና ክፍተቶች ላይ ትኩረት ተሰጥቷል።

​የሆስፒታሉ አመራሮች ከተሳታፊዎች ለተነሱ ጥያቄዎችና አስተያየቶች ምላሽና ማብራሪያ የሰጡ ሲሆን፣ በቀጣይም የጤና መድህን ተጠቃሚዎች ያለምንም እንግልት ጥራት ያለው የሕክምና አገልግሎት እንዲያገኙ የክትትልና ቁጥጥር ሥርዓቱ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አቅጣጫ አስቀምጠው ውይይቱ ተጠናቋል።

የደባርቅ ጠቅላላ ሆስፒታል የሚያዚያ ወር የሥራ አፈጻጸም ግምገማ አካሄደ​ደባርቅ 30/08/2018 የደባርቅ ጠቅላላ ሆስፒታል የአገልግሎት አሰጣጡን ጥራት ለማረጋገጥና ተቋማዊ አሰራሩን ለማጠና...
08/05/2026

የደባርቅ ጠቅላላ ሆስፒታል የሚያዚያ ወር የሥራ አፈጻጸም ግምገማ አካሄደ

​ደባርቅ 30/08/2018

የደባርቅ ጠቅላላ ሆስፒታል የአገልግሎት አሰጣጡን ጥራት ለማረጋገጥና ተቋማዊ አሰራሩን ለማጠናከር የሚያስችለውን ወርሃዊ የሥራ አፈጻጸም ግምገማ (PMT) ዛሬ አካሂዷል።

​በመድረኩ ላይ የቀረበው የሚያዚያ ወር የሥራ ሪፖርት በሁለት ዋና ዋና ክፍሎች ተከፍሎ የታየ ሲሆን፤ የመጀመሪያው በመጋቢት ወር ግምገማ ወቅት የታዩ ክፍተቶችን ለመሙላት በወጣው ዕቅድ (Action Plan) መሠረት የተከናወኑ ተግባራት አፈጻጸም ላይ ያተኮረ ነበር። ሪፖርቱን ያቀረቡት አቶ ማሙዬ ገብረመድኅን ባለፈው ወር እንዲስተካከሉ አቅጣጫ የተቀመጠላቸው ጉዳዮች በምን ደረጃ ላይ እንደሚገኙና በወርሃ የሚያዚያ የተመዘገቡ መደበኛ የሥራ ውጤቶች በዝርዝር ቀርበዋል።

​ሪፖርቱን መነሻ በማድረግ የሆስፒታሉ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ አለአምላክ ተስፋ እና ሜዲካል ዳይሬክተሩ ዶክተር ፍቃዴ አማረ ከሠራተኞችና ከክፍል ኃላፊዎች ጋር ሰፊ ውይይት አድርገዋል። በውይይቱ ወቅትም በወሩ ውስጥ የታዩ ጠንካራ ጎኖች ተጠናክረው እንዲቀጥሉና በግምገማው የታዩ ደካማ አፈጻጸሞች ደግሞ በምን መልኩ መታረም እንዳለባቸው የጋራ መግባባት ላይ ተደርሷል።

​የመድረኩ ተሳታፊዎች በበኩላቸው በሥራ ሂደት ላይ የሚያጋጥሟቸውን ተግዳሮቶች በማንሳት ጥያቄዎችንና የመፍትሔ ሐሳቦችን ያቀረቡ ሲሆን፣ ለአስተያየቶቹም በአወያዮቹ በኩል ዝርዝር ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቷል።

​በመጨረሻም የሆስፒታሉ አመራሮች በቀጣይ የሥራ ጊዜያት አገልግሎቱን ይበልጥ ቀልጣፋና ተደራሽ ለማድረግ የሚያስችሉ ግልጽ የሥራ አቅጣጫዎችን በማስቀመጥ መርሃ ግብሩን አጠናቀዋል።

"ለነገዋ እናት ዛሬ እንድረስላት፦ በስሜን ጎንደር ዞን ጤና መምሪያ የHPV ክትባትና የቅድመ መከላከል ንቅናቄ"​(ደባርቅ 30/08/2018)በኢትዮጵያ በየዓመቱ በሺዎች የሚቆጠሩ እናቶችን ለህ...
08/05/2026

"ለነገዋ እናት ዛሬ እንድረስላት፦ በስሜን ጎንደር ዞን ጤና መምሪያ የHPV ክትባትና የቅድመ መከላከል ንቅናቄ"
​(ደባርቅ 30/08/2018)
በኢትዮጵያ በየዓመቱ በሺዎች የሚቆጠሩ እናቶችን ለህልፈት የሚዳርገው የማህፀን በር ካንሰር (Cervical Cancer)፣ በአሁኑ ወቅት የህዝብ ጤና ስጋትነቱ አሳሳቢ ደረጃ ላይ ደርሷል። ይህንን አደጋ ለመቀልበስ የሰሜን ጎንደር ዞን ጤና መምሪያ ከአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ጤና ቢሮ ጋር በመተባበር፣ በሽታውን በመከላከል ረገድ አዲስ ምዕራፍ የሚከፍት የሶስት ቀናት የሴንሲታይዜሽን (Sensitization) ወርክሾፕ ከሚያዝያ 28 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በደባርቅ ከተማ እያካሄደ ይገኛል።

​"ህመምን ከማከም የሞት ምክንያትን በክትባት መከላከል" በማለት ​የመድረኩን የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የሰሜን ጎንደር ዞን ጤና መምሪያ ምክትል ኃላፊ አቶ ልዑል ብርሃን፣ በሽታው በግለሰብ ጤና፣ በቤተሰብ እና በሀገር ኢኮኖሚ ላይ እያደረሰ ያለው ጉዳት ከፍተኛ መሆኑን ገልጸዋል። "የማህፀን በር ካንሰር በርካታ እናቶቻችንን ያለጊዜያቸው ለህመምና ለሞት እየዳረገ ያለ የጤና ችግር ነው" ያሉት አቶ ልዑል፣ ይህንን ስቃይ ለመግታት ከመቼውም ጊዜ በላይ ትኩረት ሰጥቶ መስራት እንደሚገባ አፅንዖት ሰጥተዋል።

​ኃላፊው አክለውም፣ እስካሁን በዘመቻ መልክ ብቻ ሲሰጥ የነበረውን የሂውማን ፓፒሎማ ቫይረስ (HPV) ክትባት፣ አሁን ላይ በመደበኛው የክትባት ፕሮግራም (Routine Immunization) ውስጥ በማካተት በቋሚነት ለህብረተሰቡ ተደራሽ ለማድረግ መታቀዱን ይፋ አድርገዋል። ይህም እናቶች ወደ ጤና ተቋማት ሲመጡ ብቻ ሳይሆን፣ በሽታው ሳይከሰት አስቀድሞ ለመከላከል የተያዘ ታላቅ ስትራቴጂ መሆኑን ጠቁመዋል።

​በዚህ ወርክሾፕ ላይ በሰፊው ትንታኔ የተሰጠበት ነጥብ፣ ክትባቱ በተለይ እድሜያቸው ከ9 እስከ 14 ዓመት ለሆኑ ሴት ልጃገረዶች መሰጠቱ ያለውን ፋይዳ ነው። በህክምና ሳይንስ ጥናቶች መሰረት:-

​ከፍተኛ መከላከያ አቅም፦ በዚህ የእድሜ ክልል ውስጥ ያሉ ልጃገረዶች ለቫይረሱ ከመጋለጣቸው በፊት ክትባቱን ሲወስዱ፣ ሰውነታቸው የሚፈጥረው የመከላከል አቅም እጅግ ከፍተኛ ነው።

​ለወደፊት ትውልድ ዋስትና፦ አሁን ላይ ልጃገረዶችን መከተብ፣ ከ20 እና 30 ዓመታት በኋላ ሊከሰት የሚችለውን የማህፀን ካንሰር ወረርሽኝ ዛሬውኑ መቁረጥ ማለት ነው።

​በመድረኩ ላይ እንደተገለጸው፣ ስራው በክትባት ብቻ የሚወሰን ሳይሆን ሶስት ዋና ዋና የትኩረት አቅጣጫዎችን የያዘ ነው፦

​ግንዛቤ ማስፋፋት፦ በህብረተሰቡ ውስጥ ስለ በሽታው ያለውን የተሳሳተ አመለካከት በመቀየር፣ ወላጆች ልጆቻቸውን በልበ ሙሉነት ለክትባት እንዲያመጡ መስራት።

​ቀደም ብሎ መለየት (Screening)፦ በአሁኑ ወቅት በበሽታው የተያዙ እናቶችን በምርመራ በመለየት፣ ካንሰሩ ገና በጅምር ላይ እያለ የህክምና እርዳታ እንዲያገኙ ማድረግ።

​የተቀናጀ ቅንጅት፦ የጤና ባለሙያዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ መምህራን እና የአካባቢ አመራሮች በጋራ በመቀናጀት ለዘመቻው ስኬታማነት እንዲሰሩ ጥሪ ቀርቧል።

​ይህ በደባርቅ ከተማ እየተካሄደ ያለው ወርክሾፕ፣ በሰሜን ጎንደር ዞን የሚገኙ እናቶችና ሴት ልጃገረዶች ከማህፀን በር ካንሰር ስጋት ነፃ እንዲሆኑ ለማድረግ የተጀመረ ታላቅ የጤና ጉዞ ነው። የጤና አመራሩ ቁርጠኝነት እና የባለሙያው ዝግጁነት ተደምሮ፣ በሽታው በዞኑ የሚያደርሰውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ኪሳራ በከፍተኛ ደረጃ ይቀንሳል ተብሎ ይጠበቃል።

​"መከላከል ከመታከም ይሻላል፣ የነገ እናቶቻችንን ጤና እንጠብቅ!"

08/05/2026

Address

Debark
Debark'

Telephone

+251907157908

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Debark General Hospital posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Debark General Hospital:

Share