Debark General Hospital

Debark General Hospital This is Debark General Hospital official page

ደባርቅ የቱሪዝምና የልማት አቅሟን ወደ ተጨባጭ ውጤት ለመቀየር አዲስ የልማት ጉዞ ጀመረችየሰሜን ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ መዳረሻ የሆነችው ደባርቅ ከተማ፣ ያላትን የተፈጥሮ፣ የታሪክና የቱሪዝም ...
12/08/2026

ደባርቅ የቱሪዝምና የልማት አቅሟን ወደ ተጨባጭ ውጤት ለመቀየር አዲስ የልማት ጉዞ ጀመረች

የሰሜን ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ መዳረሻ የሆነችው ደባርቅ ከተማ፣ ያላትን የተፈጥሮ፣ የታሪክና የቱሪዝም ሀብት በአግባቡ በመጠቀም ከተማዋን የተሻለ የቱሪዝምና የልማት ማዕከል ለማድረግ እና የቱሪዝም ዘርፉን ለማነቃቃት አዲስ የልማት እንቅስቃሴ ጀምራለች።

ደባርቅ በተፈጥሮ የታደለች ከተማ ከመሆኗ ባሻገር፣ በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኘው ብርቅዬው ዋልያ፣ የተለያዩ የዱር እንስሳትና አእዋፋት እንዲሁም ሀገር በቀል እጽዋት የሚገኙበት የሰሜን ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ መግቢያ በመሆኗ ከፍተኛ የቱሪዝም አቅም አላት።

የሰሜን ጎንደር ዞን ዋና ከተማ የሆነችው ደባርቅ፣ በራስ ደጀን ተራራና በሊማሊሞ ጠመዝማዛ መንገድ የተከበበች ሲሆን፣ በአካባቢዋ የሚገኙ የተፈጥሮና የቱሪዝም ሀብቶች ከከተማዋ አቅም ጋር ተጣጥመው እንዲለሙ የልማት ሥራዎች መጀመራቸው ተገልጿል።

በመላ ሀገሪቱ እየተካሄደ ያለው የኮሪደር ልማትም ለደባርቅ ያላትን እምቅ አቅም ወደ ተጨባጭ የልማት ውጤት ለመቀየር ትልቅ ዕድል እንደሆነ ተጠቁሟል።

ይህንን የልማት ጉዞ ለማጠናከር የከተማዋ ነዋሪዎችም በሰላም ማስጠበቅ ላይ ያሳዩትን ተሳትፎ ወደ ልማት በማሸጋገር ንቁ ሚና እንዲወጡ ጥሪ ቀርቧል።

የደባርቅን የቱሪዝም አቅም፣ የሰሜን ተራሮች ብሔራዊ ፓርክንና በአካባቢው የሚገኙ ቅርሶችን ለመጠበቅና ለማልማት የሚያግዝ የምክክር መድረክም ተዘጋጅቷል።

“ቅርሶቻችንን እንንከባከብ፤ የወደፊታችንን እንገንባ!” በሚል መሪ ሀሳብ የሚካሄደው ይህ መድረክ፣ ነሐሴ 18 ቀን 2018 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ሂልተን ሆቴል ከ12፡00 ሰዓት እስከ ምሽት 2፡00 ሰዓት በታላቅ ድምቀት እንደሚካሄድ ተገልጿል።

በመድረኩ የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ፕሬዚዳንት ክቡር ታዬ አጽቀሥላሴ የክብር እንግዳ ሆነው እንደሚገኙ መረጃው ያመለክታል።

መድረኩ የሰሜን ተራሮች ብሔራዊ ፓርክንና ደባርቅን በማልማት፣ ቅርሶችን በመጠበቅና የአካባቢውን የቱሪዝም አቅም በማሳደግ ረገድ የሕዝብ፣ የተቋማትና የባለድርሻ አካላትን ትብብር ለማጠናከር የጋራ አቅጣጫ ለማስቀመጥ ያለመ ነው።

ደባርቅ ያላትን የተፈጥሮ፣ የታሪክና የቱሪዝም ፀጋ ከተገቢው ጥበቃና ልማት ጋር በማጣመር ወደ ዘላቂ የኢኮኖሚና የከተማ ልማት ለመቀየር የጀመረችው ጉዞ የከተማዋን ነገ የበለጠ ተስፋ ሰጪ ሊያደርግ እንደሚችል ተገልጿል።

በዚህ ጥረት የደባርቅ ተወላጆች፣ ነዋሪዎችና ደጋፊዎች ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑም ተጠቁሟል።

11/08/2026
"936 ታካሚዎች ከፍተኛ የቀዶ ህክምና አገልግሎት አግኝተዋል፣ለ2788 እናቶች የወሊድ አገልግሎት የተሰጠ ሲሆን 446 ወላድ እናቶች ደግሞ በቀዶ ጥገና (Cs) በአንድ ዓመት ውስጥ እንዲወልዱ...
11/08/2026

"936 ታካሚዎች ከፍተኛ የቀዶ ህክምና አገልግሎት አግኝተዋል፣ለ2788 እናቶች የወሊድ አገልግሎት የተሰጠ ሲሆን 446 ወላድ እናቶች ደግሞ በቀዶ ጥገና (Cs) በአንድ ዓመት ውስጥ እንዲወልዱ ተደርጓል" አቶ አለአምላክ ተስፋ የደባርቅ ጠቅላላ ሆስፒታል ዋና ስራ አስኪያጅ
ደባርቅ ጠቅላላ ሆስፒታል የ2018 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈጻጸም በ05/12/18 ገመገመ።
(ደባርቅ 05/12/18)
ደባርቅ ጠቅላላ ሆስፒታል የ2018 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ አካሂዷል። በግምገማው የሆስፒታሉ የማኔጅመንት አባላት፣ ኬዝ ማናጀሮች፣ የክፍል አስተባባሪዎች፣ የስራ ሂደት መሪዎች፣ ፎካል ፐርሰኖች እንዲሁም ከየስራ ክፍሉ የተጋበዙ ባለሙያዎች ተሳታፊ ሆነዋል።
ዓመታዊ የአፈጻጸም ሪፖርቱን ያቀረቡት የፕላንና ፕሮግራም ባለሙያ የሆኑት አቶ ሐዋርያት ማሙዬ ሲሆኑ በሪፖርታቸው ሆስፒታሉ በ2018 በጀት ዓመት ውስጥ ለ89,723 ተመላላሽ ታካሚዎች ህክምና መስጠቱን ገልጸዋል፤ ይህ አሃዝ ሆስፒታሉ ለማህበረሰቡ ካለው ተደራሽነትና ተቀባይነት አንጻር በጤናው ዘርፍ ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ መሆኑን ያመላክታል። በተጨማሪም ለ936 ታካሚዎች ከፍተኛ የቀዶ ህክምና አገልግሎት፣ ለ223 ታካሚዎች ደግሞ መለስተኛ የቀዶ ጥገና አገልግሎት መሰጠቱን አብራርተዋል፤ ይህም ሆስፒታሉ ውስብስብና ደረጃውን የጠበቀ የቀዶ ህክምና አገልግሎት በመስጠት የታካሚዎችን ህይወት እየታደገ መሆኑን ገልፀዋል።
በእናቶችና ህጻናት ጤና ረገድ፣ ለ2197 ነብሰጡር እናቶች የእርግዝና ክትትል፣ ለ2788 ወላድ እናቶች የወሊድ አገልግሎት፣ እንዲሁም ለ446 ወላድ እናቶች በቀዶ ጥገና (CS) የመውለድ አገልግሎት መሰጠቱ ተጠቅሷል። የCS ወሊድ መጠን መጨመር በአንድ በኩል ውስብስብ የወሊድ ጉዳዮችን በወቅቱ የመለየትና ህይወት የማዳን አቅምን የሚያሳይ ሲሆን፣ በሌላ በኩል ደግሞ ተቋሙ በቂ የማህፀንና ፅንስ ስፔሻሊስት ሐኪም ባለመኖሩ በተወሰነ የሰው ኃይል ላይ ጫና እየፈጠረ እንደሆነ አመላካች ነው። ለዚህም የሆስፒታሉ የተቀናጀ የድንገተኛ የቀዶ ጥገና ባለሙያ የሆኑት IESO ማሙሽ አቡሃይ በ2018 ዓመቱን ሙሉ ለ24 ስዓት ያለእረፍት በሆስፒታሉ ውስጥ ውለው በማደር ለእናቶችና ድንገተኛ አደጋ ለደረሰባቸው ሁሉ የህክምና አገልግሎት በመስጠታቸው ሆስፒታሉ ታላቅ ምስጋና በተቋሙና በህዝብ ስም አቅርቦላቸዋል። በሪፖርቱ ለ385 በፅኑ ህመም ለተያዙ ጨቅላ ህጻናት ህክምና መሰጠቱም ተጠቅሷል፤ ይህ የኒዮናታል ኬር አገልግሎት ጥራትና ተደራሽነት ላይ ትልቅ አስተዋጽኦ ማድረጉን ያሳያል።
ሪፖርቱ አክሎም ለ217 ሴቶች የማህፀን በር ካንሰር ምርመራ ማግኘታቸውን፣ ለ4275 ታካሚዎች የዓይን ህክምና መሰጠቱን፣ለ136 ፆታዊ ጥቃት ለደረሰባቸው የአንድ ማዕከል አገልግሎት ማግኘታቸውን፣ ለ2059 የስነ አዕምሮ ታካሚዎች የህክምና አገልግሎት መሰጠቱን፣ ለ4010 ታካሚዎች ከ3 ቀናት በላይ በሆስፒታሉ ተኝተው ህክምና ማግኘታቸውን፣ ለ10,222 የድንገተኛ ህክምና ላስፈለጋቸው ታካሚዎች በድንገተኛ ክፍል ህይወት አድን ህክምና መሰጠቱን ገልጿል፤ ይህ ከፍተኛ ቁጥር ተቋሙ ያለበትን የስራ ጫናና ለድንገተኛ ጉዳዮች ያለውን ዝግጁነት በግልጽ ያመላክታል።
በተጨማሪም ለ998 የART ህክምና ተከታታዮች እና ለ77 የቲቢ ታካሚዎች ሙሉ ህክምና መሰጠቱን፣ ለ3716 ህፃናት የክትባት አገልግሎት ማግኘታቸውን፣ ለ2522 ተገልጋዮች የቤተሰብ ምጣኔ አገልግሎት በተለያዩ አማራጮች መሰጠቱ ተጠቅሷል፤ እነዚህ አገልግሎቶች የተላላፊ በሽታ መከላከልና የስነ ተዋልዶ ጤና አገልግሎት ዘላቂነትን ከማረጋገጥ አኳያ ወሳኝ ናቸው።
ከጎንደር ደም ባንክ ጋር በመተባበር 470 ከረጢት ደም ደባርቅ ላይ መሰብሰቡ እና ከዚህ ውስጥ 382 ከረጢት ደም ለደም ማነስና ለደም መፍሰስ ችግር ለተጋለጡ ወገኖች በደባርቅ ጠቅላላ ሆስፒታል ውስጥ መለገሱ ተገልጿል፤ ይህም ሆስፒታሉ ከአካባቢው የደም ባንክ ጋር በቅንጅት እየሰራ መሆኑን ያመለክታል።
የሆስፒታሉ ዓመታዊ የፋይናንስና የግዥና የንብረት አስተዳደር ሪፖርት በስራ ሒደት አስተባባሪ በሆኑት በአቶ ቴዎድሮስ ሙሉሰው ቀርቧል። በሪፖርቱም ጥቅል የበጀት አጠቃቀም እና የግዥ ሪፖርት ቀርቧል። በተጨማሪም ሆስፒታሉ በዓመቱ የ 20,264,053.53 ብር የመድኃኒት ግዥ የተፈፀመ ሲሆን የ 15,823,235.64 ብር የሚያወጡ የተለያዩ መድኃኒቶች እና የህክምና መሳሪያዎች ሆስፒታሉ በድጋፍ ከአጋር አካላት በድጋፍ ያገኘ ሲሆን የ 5,050,010.62 ብር ነፃ የህክምና አገልግሎት ለወላድ እናቶችና ለህፃናት ተሰጥቷል፣ ለጤና መድህን ተጠቃሚዎች የ 18,603,143.16 ብር የሚያወጣ ህክምና ተሰጥቷል፣ የተሽከርካሪ አደጋ ለደረሰባቸው ድንገተኛ የአካል ጉዳት ለደረሰባቸው የ 318,969.50 ብር ነፃ የህክምና አገልግሎት ተሰጥቷል፣ ለተፈናቃዮች እና ለፀጥታ አስከባሪ አባላት የ 792,024 ብር የህክምና አገልግሎት ተሰጥቷል፣ ለጤና ሴክተር ሰራተኞች የ 374,274.99 ብር ህክምና የተሰጠ መሆኑ ተገልጿል።
የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ደግሞ በፕላንና ፕሮግራም አስተባባሪ በሆኑት በአቶ ማሙዬ ገ/መድኅን ቀርቧል።
የቀረቡትን ሪፖርቶች እና ዕቅድ መሰረት በማድረግ የሆስፒታሉ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ አለአምላክ ተስፋ እና ሜዲካል ዳይሬክተሩ ዶክተር ፍቃዴ አማረ ተሰብሳቢዎችን ያወያዩ ሲሆን፣ ተሳታፊዎቹ የተቋሙን አገልግሎት ሊያሻሽሉ የሚችሉ ሐሳቦችን፣ አስተያየቶችንና ጥያቄዎችን አቅርበዋል። አቶ አለአምላክ ተስፋ "በውስን የሰው ኃይል ለ936 ሰዎች ከፍተኛ የቀዶ ህክምና አገልግሎት መስጠታችን፣ 446 ወላድ እናቶች በቀዶ ህክምና በደባርቅ ሆስፒታል እንዲወልዱ ማድረጋችን እና እያንዳንዱ የተሰጠው የጤና አገልግሎት የሚያመላክተው ሆስፒታሉ ምን ያህል ከፍተኛ ቁጥር ያለው የሰዎችን ህይወት እየታደገ እንዳለ ያሳያል" ብለዋል።
በሆስፒታሉ የሰው ኃይል እጥረት ቢኖርም ይህን ያህል ውጤት ማስመዝገብ የተቋማዊ አመራርና የሰራተኞች ቁርጠኝነት ውጤት በመሆኑ ለተቋሙ ባለሙያዎችና ሰራተኞች በሙሉ በተቋሙና በህዝብ ስም ለሰጡት ውጤታማ አገልግሎት ታላቅ ምስጋና እንደሚገባቸው ተገልጿል። ሆስፒታሉ ዘላቂ አገልግሎት አሰጣጥን ለማረጋገጥ ተጨማሪ ስፔሻሊስት ባለሙያዎችን የማሟላት አስፈላጊነት ጎልቶ ይታያል። ሆስፒታሉ የተሟላ የቀዶ ጥገና ስፔሻሊስት ሐኪም፣ የማህፀንና ፅንስ ስፔሻሊስት ሐኪም እንዲሁም ሌሎች ከፍተኛ ሐኪሞች ቢሟሉለት ከዚህ በላይ መስራት የሚችል፣ ለአካባቢው ማህበረሰብና ለሀገር ትልቅ የህክምና አገልግሎት የሊሰጥ ተቋም መሆኑን በመግለጽ፣ ከተሰብሳቢዎቹ የተነሱ ጉዳዮች በመድረክ መሪዎቹ ሰፊ ማብራሪያና ምላሽ ተሰጥቷቸዋል።
በመጨረሻም የሆስፒታሉ መሪዎች፣ ደባርቅ ጠቅላላ ሆስፒታል ከመንግስት በሚመደብለት በጀት፣ በውስጥ ገቢ ከሚሰበስበውና ከህዝብ ተሳትፎና ከአጋር አካላት የሚሰበሰብ ሀብትን በመጠቀም ሆስፒታሉን ለታካሚዎችና ለተቋሙ ሰራተኞች ምቹ ለማድረግ እንደሚሰራ ገልጸው፣ ለ2019 ዓ.ም ጥራት ያለው የህክምና አገልግሎት መስጠት የሚያስችሉ ዝርዝር የስራ ዕቅዶች፣ መመሪያዎችና አቅጣጫዎችን አስቀምጠዋል።
ደባርቅ ጠቅላላ ሆስፒታል ለስሜን ጎንደር ህዝብ ከፍተኛውን የጤና አገልግሎት እየሰጠ የሚገኝ አንጋፋ ተቋም በመሆኑ ሆስፒታሉ በ2019 ዓ.ም የጤና መረጃ አያያዙን ዲጂታላይዝ ለማድረግ፣ የመድኃኒት እጥረትና የላቦራቶሪ ምርመራዎች ለማሟላት፣ የሰው ኃይል እጥረትን ለመፍታት በተለይም የከፍተኛ ስፔሻሊስት ሐኪሞችንና ጠቅላላ ሐኪሞችን (ሜዲካል ዶክተሮችን) ለማሟላት፣ ሙያተኞች የሚያነሷቸው የመብትና የጥቅማጥቅም ጥያቄዎች እንዲመለሱ፣ ሆስፒታሉ መብራት ሲጠፋ ከነዳጅ ተጠቃሚነት ተላቆ የሶላር ኢነርጅ ተጠቃሚ እንዲሆን፣ ደረጃውን የጠበቀ ማስፋፊያ ግንባታ እንዲደረግለት ሁሉም ባለድርሻ አካላት ሆስፒታሉ የሚሰጠውን ጥራት ያለው የጤና አገልግሎት ከዚህ በላይ ማስቀጠል እንዲችል ከፍተኛ እገዛና ርብርብ እንዲያደርጉ ጥሪ ቀርቧል።

07/08/2026

‎የአማራ ክልል የ2018 ዓ.ም የክረምት ነፃ የጤና በጎ ፈቃድ አገልግሎት በተጠናከረ ሁኔታ ቀጥሏል

‎​የአማራ ክልል ጤና ቢሮ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ቴክኒካል ኮሚቴ በክላስተር በመከፋፈል በየዞኑ የተከናወኑ ተግባራትን አጠቃላይ እንቅስቃሴ በአካል በመገኘት ድጋፍና ክትትል ያደረገበት ሪፓርት ተገመገመ።

‎ድጋፍ በ2018 የክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ቅድመ ዝግጅት እና ትግበራ ምዕራፍ ሊከናወኑ በሚገባቸው ተግባራት ላይ ትኩረት ያደረገ ሲሆን በተጠናከረ ቼክ ሊስት የተደረገው ድጋፍ በተጨማሪም የተለያዩ የኢኒሼቲቭ ስራዎችን፣ የዜጎች የበጎ ፍቃድ አገልግሎቶችን እና ምርጥ ተሞክሮዎችን በተቋማቱ ተዘዋውሮ በመመልከት አስፈላጊውን ሙያዊ ድጋፍ ያደረጉ መሆኑን ከሪፓርቱ መገንዘብ ተችሏል።

‎የኮሚቴው አስተባባሪ ዶር ትግስት ብሩ በበኩላቸው የድጋፉ ዋና አላማ ከእቅድ ዝግጅት ጀምሮ እስከ አተገባበር ያሉ በክረምት ወቅት የሚሰሩ የጤና ስራዎችን በአግባቡ በመምራት የበጀት ዓመቱን እቅድ ውጤታማ ማድረግ መሆኑን ገልጸዋል።

‎ በጤናው ዘርፍ የታዩ አፈጻጸሞች ለክልሉ በሞዴልነት የሚጠቀሱ ምርጥ ተሞክሮዎች መሆናቸውን እና አጠቃላይ የቅንጅት ስራው አበረታች እንደነበርና የህብረተሰቡን ጤና ከማስጠበቅ አኳያ ጠቀሜታው ሰፊ ነው ያሉት ዶክተር ትግስት በቀጣይም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል።

‎ ​የክትትልና ድጋፍ ኮሚቴው በሁሉም ክላስተር ተግባራትን አስመልክቶ የማጠቃለያ ውይይት አካሂዷል።

‎​በውይይቱ በየጤና ተቋማቱ የታዩ ጥንካሬዎችን እና በቀጣይ ትኩረት ሊሰጣቸው የሚገቡ አቅጣጫዎችን አስቀምጠዋል።

‎ #አብክመጤናቢሮ


‎ነሀሴ 01/2018ዓ.ም
‎​

07/08/2026
የደባርቅ ጠቅላላ ሆስፒታል የሐምሌ ወር የሥራ አፈጻጸም ግምገማ አካሄደ የደባርቅ ጠቅላላ ሆስፒታል የአገልግሎት አሰጣጡን ጥራት ለማረጋገጥና ተቋማዊ አሰራሩን ለማጠናከር የሚያስችለውን ወርሃዊ ...
06/08/2026

የደባርቅ ጠቅላላ ሆስፒታል የሐምሌ ወር የሥራ አፈጻጸም ግምገማ አካሄደ
የደባርቅ ጠቅላላ ሆስፒታል የአገልግሎት አሰጣጡን ጥራት ለማረጋገጥና ተቋማዊ አሰራሩን ለማጠናከር የሚያስችለውን ወርሃዊ የሥራ አፈጻጸም ግምገማ (PMT) የስራ ክፍል አስተባባሪዎች እና ሙያተኞች በተገኙበት አካሂዷል።
​በመድረኩ ላይ የቀረበው የሐምሌ ወር የሥራ ሪፖርት በአቶ ማሙዬ ገብረመድኅን የቀረበ ሲሆን ​ሪፖርቱን መነሻ በማድረግ የሆስፒታሉ ተወካይ ሥራ አስኪያጅ እና ሜዲካል ዳይሬክተሩ ዶክተር ፍቃዴ አማረ ከሙያተኞችና ከክፍል ኃላፊዎች ጋር ሰፊ ውይይት አድርገዋል። በውይይቱ ወቅትም በወሩ ውስጥ የታዩ ጠንካራ አፈፃፀም ያላቸው ተግባራት ተጠናክረው እንዲቀጥሉና በግምገማው የታዩ ደካማ አፈጻጸሞች ደግሞ በምን መልኩ መታረም እንዳለባቸው የጋራ መግባባት ላይ ተደርሷል።
​የመድረኩ ተሳታፊዎች በበኩላቸው በሥራ ሂደት ላይ የሚያጋጥሟቸውን ተግዳሮቶች በማንሳት ጥያቄዎችንና የመፍትሔ ሐሳቦችን ያቀረቡ ሲሆን፣ ለአስተያየቶቹም በአወያዮቹ በኩል ዝርዝር ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቷል።
​በመጨረሻም የሆስፒታሉ አመራሮች በቀጣይ የሥራ ጊዜያት የህክምና አገልግሎቱን ይበልጥ ቀልጣፋና ተደራሽ ለማድረግ የሚያስችሉ ግልጽ የሥራ አቅጣጫዎችን በማስቀመጥ መርሃ ግብሩን አጠናቀዋል።

‎የጡት ማጥባት አስፈላጊነት እና ጥቅሞች‎የጡት ማጥባት ለሕፃናት ጤናማ እድገትና የበሽታ መከላከል አቅም እንዲሁም ለእናቲቱ ጤና እጅግ አስፈላጊ የሆነ ተፈጥሯዊ ሂደት ነው። ህጻናት በመጀመሪያ...
06/08/2026

‎የጡት ማጥባት አስፈላጊነት እና ጥቅሞች
‎የጡት ማጥባት ለሕፃናት ጤናማ እድገትና የበሽታ መከላከል አቅም እንዲሁም ለእናቲቱ ጤና እጅግ አስፈላጊ የሆነ ተፈጥሯዊ ሂደት ነው። ህጻናት በመጀመሪያዎቹ 6 ወራት የእናት ጡት ወተት ብቻ (Exclusive Breastfeeding) ማግኘት አለባቸው።
‎👉በጡት ማጥባት ወቅት ትኩረት ሊደረግባቸው የሚገቡ፦
‎▪️የመጀመሪያውን ወተት (እንገር / Colostrum) ለህጻኑ ይስጡ:- እንገር የመጀመሪያው የእናት ወተት ሲሆን ሕፃኑን ከበሽታዎች የሚጠብቅ በጣም ከፍተኛ የመከላከያ ኃይል ያለው ነው። ይህ ወተት ከፍተኛ የበሽታ መከላከል አቅም ያላቸውን ንጥረ ነገሮች ይዟል።
‎▪️ጡት ማጥባትን በመጀመሪያው 1 ሰዓት ውስጥ ይጀምሩ:- ሕፃኑ ከተወለደ በኋላ በመጀመሪያው 1 ሰዓት ውስጥ ጡት ማጥባት መጀመር ለሕፃኑ ሕይወት ማዳን፣ ለእናቱም ፈጣን ማገገም ይረዳል። እንዲሁም የጡት ወተት ምርት በቶሎ እንዲጀምር እና በቂ የሆነ ወተት እንዲመነጭ ያደርጋል።
‎▪️ህጻኑ/ኗ በፈለገ/ች ጊዜ ያጥኑ:- ሕፃኑ/ኗ በፈለገ/ች ጊዜ በቀንና በሌሊት በተደጋጋሚ ጡት ያጥቡ። ይህ የወተት ምርትን ያበረታታል።
‎▪️ትክክለኛ የማጥባት ሁኔታን ይጠቀሙ (Positioning & Latching)፦ በአግባቡ ለማጥባት እናቲቱ በተመች ሁኔታ ተቀማጣ ማጥባት አለባት። ሕፃኑ አፉን በደንብ ከፍቶ ጠቆር ያለዉን የጡትዎን ክፍል አብዛኛዉን በመጉረስ፣ ጉንጮቹ ሞላ በመድረግና በመሀል ትንሽ እያረፈ በደንብ መሳቡን ማረጋገጥ ያስፈልጋል፡፡

‎▪️ሙሉ በሙሉ በጡት ወተት ብቻ ማሳደግ፦ በመጀመሪያዎቹ 6 ወራት ውስጥ ውሃን ጨምሮ ምንም አይነት ተጨማሪ ምግብ ወይም ፈሳሽ ሳይሰጥ በጡት ወተት ብቻ ህጻናትን ማሳደግ ይገባል። ይህም የጡት ወተት በመጀመሪያዎቹ 6 ወራት ለህጻናት እድገት የሚያስፈልጉትን ንጥረ ምግቦች እንዲሁም ውሃን ስለሚይዝ ነው።

‎▪️የበሽታ መከላከል ጥቅሞች፦ የጡት ወተት ሕፃናትን ከተቅማጥ፣ ከሳንባ ነቀርሳ (Pneumonia) እና ከጆሮ ኢንፌክሽን የሚከላከል ሲሆን እናቶችንም ከጡት እና ከማህፀን ካንሰር ተጋላጭነት ይከላከላል።

‎▪️በህመም ወቅት ጨምረው ጡት ያጥቡ:- ከ 6 ወር በታች የሆኑ ህጻናት በተለያየ ህመም በሚጠቁበት ወቅት ከሌላ ጊዜ አብልጠው/ጨምረው ያጥቡ። ይህም በህመም ወቅት በሽታን ለመቋቋም እንዲሁም በቶሎ ለማገገም ይረዳቸዋል።

‎▪️ከ6 ወር ጀምሮ(181 ቀን) ከተጨማሪ ምግብ ጎን ለጎን ጡት ማጥባትን ይቀጥሉ:- ከ 181ኛ ቀን ጀምሮ እድሜውን የሚመጥን፣ የተመጣጠነና የተሰባጠረ ተጨማሪ ምግብ በመጀመር ጡት ማጥባቱን እስከ 2 ዓመት ወይም ከዚያ በላይ ይቀጥሉ።

‎▪️የበቂነት ምልክቶች፦ ሕፃኑ በቀን ቢያንስ ከ6-8 ጊዜ የሚሸና ከሆነ እና በቂ የክብደት እድገት የሚያሳይ ከሆነ፥ ህጻኑ በቂ ወተት ማግኘቱን ማረጋገጥ ይቻላል።

‎▪️የእናቶች ስነ-ምግብ ሁኔታ፦ የሚያጠቡ እናቶች ከሌላው ጊዜ ተጨማሪ ሁለት ጊዜ የተሰባጠረ ምግብ ማገኘት የሚገባዘው ሲሆን፣ በቂ ፈሳሽ (ውሃ፣ ሾርባ) እና አትክልትና ፍራፍሬዎችንም አብዝተው መመገብ ይኖርባቸዋል።

‎👉 የአባቶች እና የቤተሰብ ሚና፦
‎የቤት ውስጥ ስራዎችን ማገዝ፦ አባቶችና ቤተሰብ የሚያጠቡ እናቶችን በቤት ውስጥ ስራ በማገዝ በቂ የእረፍት ጊዜ እንዲኖራቸው ማድረግ አለባቸው።
‎‎▪️ስነ-ልቦናዊ ድጋፍ መስጠት፦ በእናቶች ላይ የሚፈጠረውን ድካም እና ጭንቀት ለመቀነስ አዎንታዊ እና ስነ-ልቦናዊ ድጋፍ ማድረግ ወሳኝ ነው።
‎‎

Address

Debark
Debark'

Telephone

+251907157908

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Debark General Hospital posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share