07/07/2023
የአዊ ብሄረሰብ አስተዳደር ጤና መምሪያ በጤና ተቋማት የሚካሄደውን የአትክልትና ፍራፍሬ የተከላ መርሐግብር ሰኔ 30/2015 ዓ/ም አስጀመረ ። የጤና መምሪያ ሀላፊ አቶ አየለ አልማው በባንጃ ወረዳ በዲንካራ ጤና ጣቢያ በመገኘት የተከላ መርሐ ግብሩን አስጀምረዋል ። በመርሐ ግብሩ የጤና መምሪያ ባለሙያዎች፣ የባንጃ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት አመራሮችና ሠራተኞች እንዲሁም የጤና ጣቢያው ባለሙያዎች ተገኝተው ተከላ አካሂደዋል።
በፕሮግራሙ ላይ ተገኝተው ተከላውን ያስጀመሩት የአዊ ብሄረሰብ አስተዳደር ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ አየለ አልማው እንደገለፁት የአገሪቱ የጤና ፓሊሲ መከላከልን መሠረት ያደረገ በመሆኑ የህክምና አገልግሎት የሚሰጡ የጤና ተቋማት ለህሙማን ምቹ ፣ ሳቢና የተስተካከለ የአየር ንብረት እንዲኖር ማድረግ አስፈላጊ በመሆኑ በብሄረሰብ አስተዳደሩ በሚገኙ አጠቃላይ የጤና ተቋማት ላይ አረንጓዴ ችግኝ ተከላ መርሀ ግብር ለማካሄድ ታቅዶ በባንጃ ወረዳ በዲንካራ ጤና ጣቢያ ማስጀመራቸዉን ተናግረዋል ።
በጤና ተቋማት የሚተከሉ ችግኞች ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸውን አትክልትና ፍራፍሬ በመትከል እና አረንጓዴ አካባቢን ለመፍጠር መሆኑን የገለፁት መምሪያ ኃላፊው በዛሬው እለት የተጀመረው የችግኝ ተከላ መርሀ ግብር በሌሎች 48 ጤና ጣቢየዎችም እንዲካሄድ መልዕክት ያስተላለፈ ሲሆን የተተከሉ ችግኞች እንዲፀድቁ የጤና ጣቢያው ማህበረሰብ የቅርብ ክትትልና ቁጥጥር እንዲያደርግ በማሳሰብ የዕለቱን መርሐግብር ተጠናቋል።
FOR A BETTER TOMORROW,PLANT MORE TREES TODAY!!!
ጤና መምሪያ (የህዝብ ግንኙነት ክፍል)
ሰኔ 30/2015 ዓ.ም