19/09/2025
_ዘመቻ_ለጤና_ባለሙያዎች_ለጤና ኤክስቴንሽን_ባለሙያዎች_እና_ለባለድርሻ_አካላት_ስልጠና_መሰጠት_ተጀመረ።
መስከረም 9/2018 ዓ.ም(ካምባ ከተማ አስ/ር ጤና ጥ/ጽ/ቤት)።
በዕለቱ መድረኩን በንግግር የከፈቱት የካምባ ከተማ አስ/ር መንግሥት ዋና ተጠሪ ፣የካምባ ዙሪያ ወረዳ ዋና አስተዳደር ፣ የካምባ ዙሪያ ወረዳ መንግሥት ዋና ተጠሪ እና የካምባ ከተማ አስተዳደር ጤና ጥ/ጽ/ቤት ኃላፍ ጨምሮ ተገኝተው የመክፈቻ ንግግር አድርጓቸዋል።
በንግግራቸው የትራኮማ በሽታ የሚያስከትለው የዓይነ ስውርነት ችግር ምን ያህል አስከፊ እንደሆነ በመረዳት የመድሐኒት ዕደላ ዘመቻው ከወትሮው በተለየ መልኩ ትኩረት ሰጥቶ ሊተግበር እንደሚገባ ጥቅሰው ለመድሃኒት ዕደላ ዘመቻ ተግባራዊነት ሁሉም የበኩሉን ድርሻ ሊወጣ እንደሚገባ አሳስበዋል።
በንግግሩ የካምባ ከተማ አስ/ር መንግሥት ዋና ተጠሪ የተከበሩ አቶ ይስሀቅ ዮሐንስ ባስተላለፉት መልዕክት
ዘመቻው በጥራትና በፍጥነት በታቀደው ልክ እንዲጠናቀቅ ሰልጣኞች ከሌሎችም የሚመለከታቸው አካላት ጋር በመቀናጀት በትኩረት ሊሰሩ እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡እንዲሁም መመሪያ መልዕክት እና ለሎችን በጤና መስክ የነበሩ ጉዳዮችን አስምሮ አንስቷል።
ቀጥሎ የካምባ ዙሪያ ወረዳ ዋና አስተዳደር የተከበሩ አቶ አዴ አለሙ የትራኮማ በሽታ መከላከያ መድሃኒት እደላው ቤት ለቤት በመጎብኘት የሚሰጥ መሆኑን ጠቁመው በዘመቻው በሁሉም ማህበረሰብ ተደራሽ እና ተጠቃሚ እንደሚሆኑም ገልጿል፡፡ አስተዳዳሪ አያይዞም ትራኮማ የዕይታ መቀነስ እና ዓይነስውርነትን የሚያስከትል በሽታ ነው ተብሏል።
በመቀጠል የካምባ ከተማ አስተዳደር ጤና ጥ/ጽ/ቤት ኃላፍ አቶ ኢዮብ ደርቤ ባስተላለፉት መልዕክት (የማህበረሰብ ዐቀፍ መድኃኒት ዕደላ ዘመቻ) zithiromax መድሃኒት የዓይን ማዝ ብቻ ሳይሆን ለሎች በርካታ በሰውነታችን ውስጥ የሚገኙ ባክቴሪያ ዓይነቶችን የማከም አቅም ያለ መድሀኒት ነው ብሏል። አያይዘውም ዘመቻው ለተከታታይ 11 ቀን የሚቆይ ስሆን ድርጅቱም ኦርቢስ እንተርናሽናል በ3 ፕሮግራሞች ዙሪያ የሚሰራ ስሆን እነርሱም :-(1) ገጠርን ያማከለ አጠቃላይ የአይን ጤና ክብካቤ።(2) በመከላከልና በማከም ላይ ያቶኮረ የአይን ጤና አገልግሎት አቅም ማጎልበት የአይን ጤና ጥናትና ግንዛቤ ማስጨበጫ።(3) እንዲሁም የአይን ማዝ በሽታ መከላከልና መቆጣጠር ስሆን የድርጅቱ ማጠንጠኛ የትራኮማን ማጥፋት ወይም ኮምፕርሄንስቭ(comprehensive) አገልግሎት መስጠት ነው ብሏል።
ኃላፍው አያይዘውም ትራኮማ (የዓይን ማዝ) በባክቴሪያ አማካይነት የሚመጣ ተላላፊ የሆነ ዓይነስውርነትን የሚያስከትል የዓይን ሕመም ስሆን የበሽታው አምጪ ተህዋስያን ቺላሚዲያ የትራኮማቲስ (chlamydia Trachomatis) እየተባለ የሚጠራ ባክቴሪያ ነው ብሏል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ MDA(mass drug administration) ማህበረሰብ አቀፍ የትራኮማ መድሃኒት ስርጭቱ አሰፈላጊ ስለሆነ ዕድሜያቸው ከ1-9 ዓመት በሆኑ ህፃናት እና የአፍለኛ ወጣቶች ላይ ትራኮማ ስርጭት ከ5% በታች መቀነስ እና ዕድሜያቸው ከ15 ዓመት በላይ በሆኑ ሰዎች ላይ የአይን ቆቦ ሽፋሽፍት ወደ ውሰጥ መቀልበስ ስርጭትን 0.2% በታች ማድረስ።
ድርጅቱ በዋናነት የሚሰራው የአይነ ስውርነት ለማጥፋት ስሆን የአለም ጤና ድርጅት ባወጣው መረጃ መሠረት በአለም ላይ ወደ 2.2 ቢሊዮን የእይታ መቀነስ ችግር ያለባቸው ሰዎች አሉ ከእነዚህ ውሰጥ ከ 1 ቢሊዮን የሚሆኑት ህክምና የሚሹ ናቸው።
#39 ሚሊዮን አይነስውር ሰዎች ይኖራሉ ከእነዚህም ውስጥ 1.4 ሚሊዮን ሕፃናት ናቸው።
#በየአመቱ 1-2 ሚሊዮን የሚሆን እየጨመረ ይገኛል።
#28 ሚሊዮን ሰዎች የሚሆኑት መከላከል ወይንም ማከም በምንችላቸው ምክንያቶች በተከሰቱ ዓይነስውርነት የተጠቁ ናቸው።
ስለዚህም በሁሉም ማህበረሰብ ክፍል ከህፃን እስከ አዋቂ ድረስ በሁሉም ቀበሌያት ላይ በከተማም ሆነ በዙሪያ መድኃኒቱን እንድትወስዱ የካምባ ከተማ አስተዳደር ጤና ጥ/ጽ/ቤት መልዕክቱን ያስተላላፋል።
በጤና ባለሙያ የሚሰጠውን መድኃኒት መውሰድ :- እናደርግ ፣ አይነስውርነትን በጋራ እንከላከል።
ምንጭ (የካምባ ከተማ አስተዳደር ጤና ጥ/ጽ/ቤት ሚዲያ )