09/09/2026
በጥቁር ዱር ጤና አጠባበቅ ጣቢያ በዛሬዉ እለት ማለትም በ04/13/2018 ዓ.ሞ የተቋሙን የ2 ወር የስራ አፈፃፀም ግምገማ አካሂዷል በግምገማዉ ሂደትም:-
👉,የጤና ጣቢያ ሀላፊ
👉,የጤና ጣቢያ የመረጃ ባለሙያ
👉,ሁሉም ባለሙያ ተገኝተዋል::
መድረኩም በጤና ጣቢያው ሀላፊ በአቶ ይልማ ጌታቸው የተመራ ሲሆን በግምገማ ሂደቱም
👉,የክትባት የጤና አገልግሎት
👉,ከ5 ዓመት በታች የህፃናት ጤና አገለግሎት
👉,የእናቶች ጤና አገልግሎት
👉,ተላላፊ እና ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች ክትትል እና ቁጥጥር ስራ የእቅድ አፈፃፀም
👉, ሪፎርም /Reform/
👉,Data Quality
👉, eCHIS የእነዚህን ተግባራቶች የ2 ወር አፈፃፀም በጥንካሬ እና በድክመት በዝርዝር ተገምግሟል::
በቀጣይ የመስከረም ወር ላይም የሩብ ዓመቱን አፈፃፀም ወደ ሚፈለገዉ ግብ ለማምጣት በድክመት የተገመገሙትን የጤና አገልግሎት ስራዎች እንደ :-
👉, የእናቶች የጤና አገልግሎት
👉,ተላላፊ እና ተላላፈ ያልሆኑ በሽታዎች ክትትል እና የቁጥጥር ስራ
👉, የሪፎርም ስራዎች
👉,የፊዚካል ፓኬጅ ቆጠራ
👉,የመረጃ ጥራትን ማዘመን ዋነኛ የርብርብ ማእከል እና የትኩረት አቅጣጫ በማድረግ እና ሌሎችንም ባለፉት 2 ወራት የተሻለ አፈፃፀም ያላቸዉን ተግባራቶች ወደ ኋላ እንዳይመለሱ አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ ቀጣይ አቅጣጫዎችን በማስቀመጥ የግምገማ ሂደቱ ተጠናቋል ::